https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/15915
በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ የሚገኙ የተለያዩ የምግብ እህልና ብጣሪ በጨረታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
  • የተለቀቀበት ቀን: ሓሙስ ሕዳር 19, 2017 (ከ 1 ዓመት)
  • መዝግያ ቀን: ሰሉስ ሕዳር 24, 2017 09:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:5%
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:50
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሰሉስ ሕዳር 24, 2017 09:15 ከሰአት
  • ምድብ: ካልኦት ዝሽወጡ/ ዘገልገሉ ኣቅሑት መሸጣ/

ጨረታ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ የሚገኙ የተለያዩ የምግብ እህልና ብጣሪ በጨረታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በቅ/ጽ/ቤቱ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

24/03/2017 ዓ.ም ከሰዓት በፊት 9፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 9፡15 ሰዓት በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ ስለዚህ ሽያጭ አፈጻጸሙ በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን እየገለጽን፣ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ የጠቅላላ የጨረታ ዋጋውን 5% በሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

ተጫራቾች ከላይ የተገለፀውን መጠን በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ። ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ ማብራሪያ በሚቀጥለው አድራሻ መጠቀም ይቻላል።

አድራሻ

ሓሚዳይ ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ ፊት ለፊት መቐለ