https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/12635
የአፋር መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ በተለያዩ መንገድ ጥገና እና መንገድ ግንባታ ሥራ ለተሰማሩ አነስተኛ ተሽከርካሪዎች እና ገልባጮች መኪኖች አገልግሎት የሚውል የተለያዩ መለዋወጫ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
  • የተለቀቀበት ቀን: ቀዳም መስከረም 16, 2013 (ከ 5 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሰሉስ መስከረም 26, 2013 10:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:1%
  • ቦታ:ኣፋር
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:200
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ረቡዕ መስከረም 27, 2013 03:00 ጥዋት
  • ምድብ: መለዋወጢ ኣቁሑት መኪና/
  • ቁጥር አ/መ/ል/ት/ቢሮ 1/2013

    ጨረታ ዝወፀሉ ዕለት  :15/1/2013

    ጨረታ ዝዕፀወሉ ዕለት:  10 ተከታታይ የሥራ ቀናት እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት
    ጨረታ ዝክፈተሉ ዕለት: በ11ኛዉ የሥራ ቀን ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት

  • ተጫራቾች የማይመለስ ብር 200 በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት ሠመራ በሚገኘው በዋና መ/ቤታችን ግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 5 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ለ2013 የታደሰ የንግድ ፈቃዳቸውን የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት እና የመንግስት መ/ቤቶች በሚፈጽሙት ግዥ ለመሳተፍ በአቅራቢዎች ዝርዝር መመዝገባቸውን የሚያረጋግጥ የምዝገባ ምስክር ወረቀት አብሮ በኢንቨሎኘ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ተጫራቾች በጨረታው ለማሳተፍ የጨረታ ማስረከቢያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ የሚያቀርቡትን ዋጋ 1 በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  • ተጫራቾች ማንኛውንም የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉበት 10 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ተብሎ አፋር መንገድ ልማት ትራንስፖር ቢሮ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 5 በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  • ጨረታው የሚቆይበት ጊዜ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ሆኖ ወዲያው ሳጥን ታሽጐ በሚቀጥለው 11ኛው የሥራ ቀን ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  • መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- ሠመራ ስልክ ቁጥር፡ 033 666 0079 መሳቁ 41

ፋክስ ቁጥር 033 666 07 54

የአፋር መንገድ ልማት ትራንስፖት ቢሮ