ግልጽ የጨረታ ማስታወቅያ
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ፍ ጽ/ቤት ERC S-EC2R project በደቡባዊ ዞን ለሚገኙ ወረዳዎች አንቡላንስ አገልግሎት የሚውሉ ጎማዎች ከነላማደርያ በቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቶች፡-
1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ
3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገባችሁ
4. በአቅራቢነት የተመዘበ
5. የማይመለስ ብር 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 10 ዘወትር በስራ ሰዓት ከ 09/06/2018 ዓ/ም እስከ 23/2018ዓ/ም መውሰድ ትችላላችሁ :
6. ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በትክክል ሞልታችሁ በማሸግ እስከ 23/06/2018 ዓ/ም ሰዓት 10፡00 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ለውድድር ለጨረታ ያቀረባቹሁት ዋጋ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ /validity period/ መጠቀስ አለበት፡፡
7. ተጫራቶች አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡
8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ብቻ 2% ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አይፈቀድም፡፡
9. የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን 23 06/2018 ዓ/ም ዓ/ም ከቀኑ 10፡30 ሰዓት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ቢገኙ
ይመረጣል፡፡ ሆኖም ግን ባለመገንኘታቸው ጨረታው አይስተጓገልም፡፡
10. አሸናፊ ተጨራቾች ጨረታው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል የማሰር ግዴታ አለበት ::
11. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፤
መመለስ