የጨረታ ማስታወቅያ
ጨረታ ሰነድ ቁጥር 002/2025/2026
ትራንስ ኢትዮጵያ ሃ/የ/የግ/ማሕበር የተለያዩ የከባድ መኪና መለዋወጫ ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመግዛት ስለፈለገ በዘርፉ የተሰማራቹ ኣቅራቢዎች ከዚህ በታች የተገለፁ ነጥቦች የምታማሉ ተጫራቶች በጨረታዉ እንድትሳተፉ እንጠይቃለን።
1. ተጫራቶች በተጠቀሰው ዘርፍ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ ኣለባቸው። የ2017 ዓ/ም ንግድፍቓድ ያላሳደሰ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል።
2. ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን በግልፅ ማስቀመጥ ኣለባቸው፡፡ ይህ ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) እንዳካተተ ተደርጎ ይወሰዳል።
3. ተጫራቶች የሚያቀርቡት ሰነድ ስርዝ ድልዝ ያለበት መሆን የለበትም፡፡ ስርዝ ድልዝ ያለበት ሰነድ ያቀረበ ተጫራች ከውድድሩ ውጭ ይሆናል።
4. ተጫራቶች ዋጋ መሙላት ያለባቸው ድርጅታችን በሰጣቸው ጨረታ ሰነድ ብቻ መሆን ኣለበት። ከዚያ ውጭ በራሳቸው ፕሮፎርማ ዋጋ የሞሉ ተጫራቶች ከውድድሩ ውጭ ይሆናሉ።
5. ተጫራቶች ነጠላ ዋጋና ድምር ዋጋ በጥንቃቄ መሙላት ኣለባቸው፡፡ ነጠላ ዋጋ ከተጠየቀው የዕቃ ብዛት (Quantity)ተባዝቶ ከሚመጣ ድምር ዋጋ ልዩነት ከተፈጠረ ነጠላ ዋጋው ትክክለኛ ተደርጎ ይወሰዳል።
6. ተጫራቶች ለጨረታ ማስከበርያ (Bid Bond) ባቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በትራንስ ኢ/ያሓ/የተ/የግ/ማሕበር ስም የተዘጋጀ ሲፒኦ ማስያዝ ኣለባቸው፡፡ ጠቅላላ ዋጋ ማለት ያቀረቡት የሁሉም ዕቃዎች ወይም የሁሉም ሞዴሎች ድምር ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) ጨምሮ ማለት ነው፡፡ የሚቀርብ ሲፒኦ ለብቻው ታሽጎ መቅረብ ኣለበት። ሲፒኦ ያላቀረበ ወይም በተጠቀሰው መጠን መሰረት ያላስያዘ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል።
7. ኣሸናፊ የሆነ ተጫራች ላሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ (ተጫማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ) ውል ማስከበርያ(Perfomance Bond) 10%ማስያዝ ኣለበት።
8. ተጫራቶች ፋይናንሻል ጨረታ ሰነድ በመቐለ በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮ እንዲሁም በአዲስ አበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል መውሰድ ኣለባቸው።
9. ተጫራቶች ኣሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀን ውስጥ ውል ማሰር ኣለባቸው።
10. ኣሸናፊ የሆኑ ተጫራቶች በአዲስ ኣበባ የተወዳደሩ ወይም በአዲስ አበባ ጨረታ ሰነድ ያስገቡ አዲስ አበባ በሚገኘው ላይዘን ኦፊስ፣ በመቐለ የተወዳደሩ ደግሞ መቐለ በሚገኘው ዋና ቢሮ በራሳቸው ማጓጓዟ ያሸነፉት ዕቃ ማቅረብ ኣለባቸው።
11. ተጫራቶች የጨረታ ሰነድ በታሸገ ፖስታ እስከ ሕዳር 02/2018 ዓ/ም ጠዋት ሰዓት 3:30 በመቐለ በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮና ኣዲስ ኣበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ፋይናንሻል ፕሮፖዛል ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ለየብቻ ማቅረብ ኣለባቸው።
12. ጨረታው ሕዳር 02/2018 ዓ/ም ጠዋት 3:30 ሰኣት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ጠዋት 4:00 ሰኣት በመቐለና በአዲስ ኣበባ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
13. የጨረታ ሰነድ በተቀመጠው የጨረታ ማስታወቅያ መሰረት የተሟላ ከሆነ ተጫራቶች ባይገኙም ይከፈታል።
14. ድርጅታችን ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
15. ለተጨማሪ ማብራርያ ወይም ግልፅ ያልሆነላቸው ሃሳብ ተጫራቶች በኣካል በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 0914 007 732 / 0911 867 040 በስራ ሰዓት ደውላቹ መጠየቅ ትችላላቹ::
ትራንስ ኢ/ያሓ/የተ/የግ/ማሕበር
መመለስ