የአካባቢ ግልፅ ጨረታ የሳር ሽያጭ ማስታወቅያ ቁጥር 001 (በድጋሚ የወጣ)
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን - መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ የሚገኝ 15.1 ሄክታር ስፋት ባለው መሬት ላይ የለማው ሳር በአካባቢ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ወይም ድርጅት ከዚህ በታች በተዘረዘረው የሳር ሽያጭ ዋጋ መነሻ መሰረት በማድረግ መግዛት ይችላል።
1) የሚሸጠው ሳር በ 15.1 ሄክታር ስፋት መሬት ላይ የለማ እና ለእንሳሳ መኖ ተስማሚ የሆነ ነው
2) ማንኛውም ተጫራች የግለሰቡ ወይም የድርጅቱ ሃላፊ ወይም ወኪል ሙሉ ስም፣ ስልክ ቁጥር እና ፊርማ በማኖር በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርበታል
3) ተጫራች ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት ቀን ጥቅምት 11 ቀን 2018 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 4፡00 ድረስ የጨረታ ስነዱን ማቅረብ ይችላል
4) ጨረታው ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጧቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመቐለ ልዮ ኢኮኖሚ ዞን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል። ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የማይገኙም ከሆነ ጨረታው ከከፈት አይታገድም።
5) የጨረታው አሸናፊ አሸናፊዎች ጨረታው ማሸነፉን ከደብዳቤ ወይም በማስታወቅያ ከተነገረው ቀን ጀምሮ በ2 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በመቐለ ልዮ ኢኮኖሚ ዞን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ተገኝቶ/ተገኝተው ውል መግባት አለበት/አለባቸው።
6) አሸናፊ ተጫራች/ተጫራቾች ውል በገባበት/በገቡበት ቀን ያሸነፉበት ዋጋ ወደ ድርጅታችን ባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ ያደርጋል/ሉ 7) የጨረታው አሸናፊ አሸናፊዎች የአሸነፈበት/ያሸነፉበት ሳር ውል ከገባበት/ከገቡበት ቀን ጀምሮ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሳሩን አጭዶ /አጭደው መውሰድ አለበት/ አለባቸው
8) የሚሸጠው ሳር ያለበት ቦታ
8.1) መደብ 1 ከማምረቻ ሼድ ቁጥር 3 ጀምሮ በምዕራብ እስከ የግቢው አጥር በደቡብ እስከ የግቢው አጥር በምስራቅ እስከ የአስፋልት መንገድ በሰሜን እስከ የአስፋልት መንገድ ድረስ
8.2) መደብ 2 ከፖሊስ ህንፃ ጀምሮ በምዕራብ እስከ የግቢው አጥር በደቡብ እስከ የአስፋልት መንገድ በምስራቅ የአስፋልት መንገድ በሰሜን የአስፋልት መንገድ ድረስ
8.3) መደብ 3 ከማምረቻ ሼድ ቁጥር 14 ጀምሮ በምዕራብ እስከ የግቢው አጥር በደቡብ እስከ የግቢው አጥር በምስራቅ እስከ የጉምሩክ ሀንፃ በሰሜን እስከ የግቢው አጥር ድረስ
8.4) መደብ 4 ከዋና በር ጀምሮ በምዕራብ እስከ የግቢው አጥር በደቡብ እስከ የአስፋልት መንገድ በምስራቅ የአስፋልት መንገድ ወደ ሰሜን ሰው ሰራሽ ሃይቅ ድረስ
9) አሸናፊ ተጫራች ተጫራቾች ውል ከገባበት/ከገቡበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ሳሩን አጭዶ/ደው : ካልወሰደዱት የከፈለው/ሉት ገንዘብ ተወርሶ ለሁለተኛ አሸናፊ ሳሩ እንዲሸጥ ይደረጋል
10) የጨረታ ውድድር የሚደረግ በእያንዳንዱ የሳር መደብ በተናጠል ይሆናል
11) ድርጅታችን የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
12) በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ በመቐለ ከተማ - ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ - ደበረገነት ቀበሌ – ማይ እሙሪ በሚባል ቦታ በሚገኘው የመቐለ ልዮ ኢኮኖሚ ዞን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ግቢ ውስጥ በአካል በመገኘት የሚሸጠውን ሳር መመልከት የሚችሉ ሲሆን ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0978192691 / 0914722381 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።