የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር MREU/004/2017
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መቐለ ሪጅን ንብረት የሆኑት የተለያዩ ቀላልና ከባድ ያገለገሉ 16 ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
1. ተጫራቾች ዝርዘር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ የሚገኝ የዛምራ ኮንስትራክሽን ህንፃ ላይ የመቐለ ሪጅን ፅ/ቤት 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 302 ቀርበው የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል ዝርዝር የተሽከርካሪዎች መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት፤ ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመቐለ ከተማ 05 ቀበሌ ደንበስኮ ፊት ለፊት የሚገኝ የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዕቃ ግምጃ ቤት ቅጥር ግቢ በመሄድ መመልከት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ ለእያንዳንዱ የጨረታ መነሻ ዋጋ 20 በመቶ (20%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) በመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት (MEKELLE REGION ELECTRIC UTILITY) ስም ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ የጨረታ ቁጥሩን በመግለፅ ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ብቻ በመቐለ ከተማ ከፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ የሚገኝ ዛምራ ኮንስትራክሽን ህንፃ 3ኛ ፎቅ የመቐለ ሪጅን ሳፕላይ ቼይን ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 304 በመምጣት ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ጨረታው ሰኔ 17 ቀን 2017ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን ከቀኑ በ9፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ከላይ በተገለፀው አድራሻ ይከፈታል።
5. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 0342406712 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
6. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፈልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የመቐለ ሪጅን ፅ/ቤት
መመለስ