ያገለገሉ እቃዎች ሽያጭ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር MWREU/003/2017
የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተለያዩ ዕቃዎችን በመቐለ ከተማ የሚገኙ (የተለያዩ ብረቶች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ያገለገሉ ጎማዎች፣ ጣውላ እንጨቶች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ባትሪዎች) ከታች በሠንጠረዡ የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ተቁ | የእቃው ዓይነት | የጨረታ መዝግያ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ መከፈቻ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ |
1 | የተለያዩ የብረት ዓይነቶች | ሰኔ 06 ቀን 2017 ዓ/ም 8፡30 | ሰኔ 06 ቀን 2017 ዓ/ም 9፡00 | 100,000 (መቶ ሺ) |
2 | ያገለገሉ የተሸከርካሪ መለዋወጫዎች | 30,000 (ሰላሳ ሺ) |
3 | ጣውላዎችና እንጨቶች | 10,000 (አስር ሺ) |
4 | ያገለገሉ የተሽከርካሪ ባትሪዎች | 10,000 (አስር ሺ) |
5 | ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማዎች | 20,000 (ሃያ ሺ) |
- ማንኛውም የንግድ ፈቃድ ያለው፣ የትኛውም አካል እና ማንኛውም የንግድ ፍቃድ የሌለው ህጋዊ ግለሰብ የጨረታ ሰነድ ገዝቶ የጨረታ ዋስትና በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮየማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺ) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- አድራሻ፡- መቐለ ከተማ ሐወልቲ ክ/ከተማ ሰማዕታት ጎደና ዛምራ ህንፃ ላይ በሚገኘው የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሳፕላይ ቼይን፣ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 304
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዡ ውስጥ በተገለፀው መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ/CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለስድስት ወራት የሚያገለግል የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ጨረታ ቁጥር MKREU/003/2017 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ሰኔ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥንው ውስጥ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9፡00 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል
- ጨረታው ከላይ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
- ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251 03 4240 6712 መደወል ይችላሉ፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
መቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት
መመለስ