አደዳይ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ
ከታወቀ እውቅና ሰጪ ተቋም እውቅና ያለው (certified ) የኦዲት ተቋም /Audit firms / በኮንትራት ለመቅጠርና ለመሾም ግልፅ ጨረታ ለማካሄድ የተዘጋጀ ሲሆን ከዚህ በታች የተጠቀሱት መመዘኛዎች የምታሟሉ እንድትወዳደሩ ድርጅታችን ይጋብዛል
- የሥራው አይነት የውጭ ኦዲተር፣
- የሥራ ዘመን ለተከታታይ ሶስት ዓመታት (2017 -2019 ዓ.ም)
- የሥራ ልምድ፣ ሶስትና በላይ ዓመት የፋይናንስ ተቋማት በኦዲት የሥራ ልምድ ያለው
- የትምህርት ደረጃ የመጀመርያ ዲግሪና ከዚህ በላይ የሆነ የኦዲት ቡድን ኣባላት ያሉት ተቋም
- የኦዲት ተቋሙ ማናጀር በፋይናንስ ተቋም በውጭ ኦዲት ሥራ የሶስት(3) ዓመታት የሥራ ልምድ ያለው መሆኑ ማስረጃ የሚያቀርብ፣
- ተጫራች የ2017 ዓ.ም የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ሥራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል፤
- የአቅራቢነት/የሙያው ምስክር ወረቀትና ንግድ ፈቃድ : ያለው
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው (TIN) ምዝገባ ቫት ሰርተፊኬት እና የወርሓዊ ሻት ድክላረስዮን ኮፒ ማቅረብ የሚችልና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትና ሌሎች በተጓዳኝ ሕጎች የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟላ የኦዲት ተቋም በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል::
በዚሁም መሰረት ቀጥሎ የተዘረዘሩ መመዘኛዎች የሚያሟላ የኦዲት ተቋም እንዲወዳደር ይጋብዛል
- ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያይዝ ባለስልጣን (AABE) የውጭ ኦዲት ለማድረግ ፈቃድ ያገኘ፣
- ኦዲተሩና አባላቱ በዓለም አቀፍ የሂሳብ ኣያያዝ (IFRS) እውቅና ካለው ተቋም ስልጠና የወሰደና ሰርቲፊኬት ያገኘ፤
- በኦዲት ተቋም ቡድን ኣባል ሆኖ የሚሰራ ኦዲተር በፋይናንስ ተቋም ኦዲት የሥራ ልምድ ያላው መሆኑ ማስረጃ የሚያቀርብ
- በኦዲት ተቋሙ/ ቡድን ኣባል ሆነው የሚሰራ ኦዲተር ኦዲት በሚያደርገው ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ቆጣቢና ተበዳሪ ያልሆነ፤
- ቀደም ሲል በማንኛውም ፍርድ ቤት በሙስና በማጭበርበር፣ ፎርጅድ ሥራ እና ሌሎች ሕጋዊ ባልሆነ ሥራዎች ያልተከሰለ፤
- የውጭ ኦዲተሩና የሥራ አጋሮቹ ወይም የሂሳብ ቡድን ኣባላት እንዲሁም ተባባሪዎች ኦዲት በሚያደርጉት ተቋም ምንም ኣይነት የተቀማጭ ሂሳብ የሌላቸው መሆኑ ማረጋገጥ ይገባዋል፤
- በታክስ ክፍያ ግዴታና ማጭበርበር ያልተከሰሰ፤
- በጥሩ የኦዲት ሥራ አፈፃፅም እውቅና ካለው አካል የድጋፍ ማረጋገጫ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል፤
- በፍርድ ቤት ያልተገባ ሥራ በመሥራቱ ኪሳራ የታወጀበት አለመሆኑ፣
- በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመርያ ቁጥር SBB/86/2023 በሚያዘው መሰረት አንድ የውጭ ኦዲተር ለእያንዳንዱ ቀጠሮ ወይም ዳግም ቀጠሮ ከላይ በተጠቀሰ መመርያ Annex I እና II መሰረት ቅደም ተከተል የሞላውን የሃቀኝነት ማረጋገጫ እና ተገቢ አዋጆ ፎርም አክብረው ጨርሰው እንዲያቀርቡ ይጠበቃል፤
- በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መስፈርቶች መሰረት / በኦዲት ውል ላይ አንድ የኦዲት ድርጅት ባለቤት፤ በዳሬክተሮችና : በሥራ አስከያጅ ላይ በሚኖር ለውጥ ምክንያት በዚህ መመርያ ላይ የተቀመጠውን መስፈርት ሳይፈፀም ከቀረ እንዲሁም በድርጅቱ ወይም በማናቸውም የሂሳብ ቡድን አባላት ላይ የሚወሰድ ማናቸውም ዲስፕሊን ወይም ህጋዊ እርምጃ ዉሉ ሊሰረዝ እንደሚችል በግልፅ መታወቅ አለበት፡
ለ. የጨረታው ቦታ አድራሻና በአየር የሚቆይበት ጊዜ
- ሰነድ ጨረታ የሚገኝበት በአዳደይ ኣነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት አድራሻ በቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 ሰምሃል መካከለኛ ሆስፒታል ፊት ለፊት
- የጨረታው ዝርዝር ዋጋ መግለጫ ከቀን 12/05/2025 ኣፈ (4/9/2017 ዓ.ም) ከጥዋት ሰዓት 2:30 እስከ ቀን 26/05/2025ኣ.ፈ(18/09/2017 ዓ.ም) ከሰአት በኋላ 11:30 በኣየር የሚቆይበትና ሰነድ የሚሸጥበት ጊዜ ይሆናል።
- ጨረታው የሚከፈተው በ26/05/2025 ኣፈ (18/09/2017 ዓ.ም) ከጥዋቱ 4:30 ቦታ በአደዳይ አነስተኛ የፋይናንስ ኢማ መ/ቤት ይሆናል።
ሐ. ተጫራቾች ተወዳዳሪ ሆነው ሲቀርቡ የሚከተለውን መመርያ ማክበር አለባቸው
- የጨረታ ሳጥን ከተዘጋ የሚመጣ ተጫራች ተቀባይነት የለውም፤
- ተወዳዳሪዎች ወይ ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ እና ኣስፈላጊ ሰነዶች በፌርማቸው የተረጋገጡና የድርጅታቸውን ማህተም ያለበት መሆን ኣለበት!
- የጨረታ ማስከበርያ 20,000.00 (ሃያ ሺ ብር) በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ CPO ማስገባት ኣለባቸው፣ የተያዘ የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታው ኣሸናፊ ውል እስኪያስር ተይዞ ይቆያል።
- የጨረታው ኣሸናፊ የሆነ ተጫራች ኣሸናፊነቱ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ በአምስትተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፈውን ለሶስት ዓመት የሚቆይ ከጠቅላላ የጨረታ ዋጋ 10% Ur conditional bank guarantee የውል ማስከበርያ በጥሬ ገንዘብ ወይም በቼክ በማስያዝ ውል ማሰር የሚችል።
- በዚህ ጨረታ ተሳታፊ ተጫራቾች ድርጅታችን ኣደዳይ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ኣማ ካዘጋጀው የፋይናንስ ጨረታ ፕሮፎርማ ቅፅ ውጪ በሌላ የፕሮፎርማ ቅፅ ሞልተው ማቅረብ ኣይፈቀድም፤ የሚቀርብ የጨረታ ኢንቨሎፕ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ተብሎ በሁለት ፖስታ መቅረብ ኣለበት፡፡
- አደዳይ ኣነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ኢማ ለሸናፊው የኦዲት ተቋም የቅድመ ክፍያ የማይፈፅም መሆኑና ክፍያ የሚፈፅመው የአንድ በጀት ዓመት ኦዲት ሥራዎች ሰርቶ ከጨረሰና የተዘጋጀው ኦዲት ሪፖርት በኢትዮጵያ የሒሳብና አያያዝ ኦዲት ቦርድ ተቀባይነት ኣግኝቶ ማህተም ተደርጎ ከለቃ ብኋላ ይሆናል።
- የተዘጋጀ የጨረታ ፕሮፎርማ ቅፅ ከአደዳይ አነስተኛ የፋይናነስ ተቋም ኢማ ዋና መስሪያ ቤት 400.00 (አራት መቶ ብር) እየከፈሉ መግዛት ይችላሉ
- ማንኛውም ተጫራች አስፈላጊ የሆኑ ማስረጃዎች ባዘጋጀው ፖስታ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
- በዚህ ጨረታ አከራካሪ ነገሮች ከተፈጠሩ መሥራታችን አደዳይ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ኢማ ጨረታው በሙሉ እና በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው!
- ለበለጠ መረጃ በሞባይል ቁጥር መ +251 91 475 4532 ወይም +251 92 672 9475 / ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
መመለስ