https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/19489

መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለምርት አገልግሎት የሚጠቀመው 22,000 ሜትሪክ ቶን Raw pet coke imported አቅራቢዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

  • የተለቀቀበት ቀን: ዓርቢ መጋቢት 4, 2018 (ከ 1 ወር)
  • መዝግያ ቀን: መጋቢት 17, 2018 03:45 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:1000000
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: መጋቢት 17, 2018 04:00 ጥዋት
  • ምድብ: ኤሌክትሮ-መካኒክስ ኣቁሑትን ግልጋሎትን/ ኬሚካልን ሪኤጀንት/

ለምርት አገልግሎት የሚውል Raw Pet coke impoted አወዳድሮ ለመግዛት ለሶስተኛ ጊዜ የወጣ

ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 02/2018

ክፍል አንድ

1. መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለምርት አገልግሎት የሚጠቀመው 22,000 ሜትሪክ ቶን Raw pet coke imported አቅራቢዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

2. በጨረታው የሚሳተፉ ድርጅቶች Import & Export በዘርፉ የተሰማሩ መሆናቸውን የሚገልፅ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸው የሚገልፅ ማስረጃ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ብር 1,000,000(አንድ ሚሊዮን ብር)በመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሃ/የተ/የግ/ማ ስም የተዘጋጀ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (cpo) ወይም ባንክ ጋራንቲ ከቴክኒካል ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከላይ በተራ ቁጥር 2 ከተጠቀሱት ማስረጃዎች ጋር በማያያዝ የድርጅታቸውን አርማና ማህተም ያለው ደብዳቤ በመፃፍ ለጨረታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

5. ተጫራቾች ከዚህ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ጋር አብሮ ከተገለፀው ዝርዝር መግለጫ መሰረት ያቀርቡትን Raw pet-coke imported በጨረታው ቀን ወይ ከዛ በፊት በራሳቸው ወጪ ለምርመራ ናሙና (ሳምፕል) ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። (ናሙናው የሚቀርበው መቀሌ በሚገኘው ፋብሪካ ይሆናል።

6. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረብያቸውና በተራ ቁጥር 2 እና 3 ላይ የተጠቀሱት ሰነዶችና በተራ ቁጥር 5 የተጠቀሰውን ናሙና (ሳምፕል) እስከ 17/07/2018 ከጠዋቱ 3፡45 ሰአት ድረስ በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ሰነዳቸውን መቀሌ በሚገኘው የፋብሪካው ዋና መስሪያ ቤት 3ኛ ፎቅ ቁጥር 115 በሚገኝ የግዥና አቅርቦት ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

7. ጨረታው በእለቱ 17/07/2018 ከጠዋቱ 3፡45 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4:00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

8. ፋብሪካው ጨረታው በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስልክ +251 344 405 806

ሞባይል +251 912 502 596

ፋስክ+251 344 405 806 /+251 344 410 863

E-mail: [email protected]

መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሃ/የተ/የግ/ማ

መቀለ