https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/19393

የሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎችን በሽረ ከተማ የሚገኙ (የተለያዩ ብረቶች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ ያገለገሉ ጎማዎች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ባትሪዎች፣ የተለያዩ ኤኤሲ ኬብሎች) ያገለገሉ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

  • የተለቀቀበት ቀን: ረቡዕ የካቲት 25, 2018 (ከ 1 ወር)
  • መዝግያ ቀን: መጋቢት 9, 2018 08:30 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:በየ ሎቱ ይለያያል
  • ቦታ:ሽረ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:1000
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: መጋቢት 9, 2018 09:00 ከሰአት
  • ምድብ: ካልኦት ዝሽወጡ/ ዘገልገሉ ኣቅሑት መሸጣ/

ያገለገሉ እቃዎች ሽያጭ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር SREU/001/2018

የሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎችን በሽረ ከተማ የሚገኙ (የተለያዩ ብረቶች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ ያገለገሉ ጎማዎች፣ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ባትሪዎች፣የተለያዩ ኤኤሲ ኬብሎች) ከታች በሠንጠረዡ የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ተ.ቁየእቃው ዓይነትየጨረታ መዝግያ ቀንና ሰዓትየጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓትየጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ
1የተለያዩ የብረት ዓይነቶችመጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ/ም 8፡30

መጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ/ም 9፡00

10,000(አስር ሺ)
2ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች5,000(አምስት ሺህ)
3ያገለገሉ የተሽከርካሪ ባትሪዎች2,000 (ሁለት ሺህ)
4ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማዎች5,000(አምስት ሺህ)
5የተለያዩ ኤኤሲ አሎሚንየም ውስጡ አቻየ ያለው5,000 (አምስት ሺህ)
6በርሚሎች1,000(አንድ ሺህ)

ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ የብረታ ብረት አቅላጭ ፋብሪካ ወይም የብረታ ብረት ማቅለጫ የንግድ ፍቃድ ያለው ግለሰብ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፣

  1. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በድርጅታችን ኣከውንት ቁጥር 1000254328058(Shire District Connection Fee) የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) ገቢ በማድረግ ዘወትር በስራ ሰዓት ሽረ ከተማ 02 ቀበሌ ግደይ ሆቴል አጠገብ ላይ በሚገኘው የሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሳፕላይ ቼይን፣ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 20 በመምጣት የሚወገዱትን ንብረቶች ዝርዝር መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፣
  2. ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ (ለ15 የስራ ቀናት) የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እሰከ 6:00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ በመሄድ መመልከት ይችላሉ፣
  3. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዡ ውስጥ በተገለፀው መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ/CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለስድስት ወራት የሚያገለግል የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
  4. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን የብረታ ብረት አቅላጭ ፋብሪካ ወይም ግለሰብ የአቅላጭ ፍቃድ መኖራቸው የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
  5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታ ቁጥር SREU/001/2018 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ መጋቢት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9፡00 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፣
  6. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን 9:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
  7. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251-0342-440336 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
  8. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ/መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት