የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

  1.  የአይቲ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች IT Electronics Equipments በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል::

በመሆኑም በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን የተዘጋጀው የጨረታ ዶኩመንት የማይመለስ ብር 100.00/አንድ መቶ ብር/ በመክፈልግንቦት 7ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ከቢሯችን የእቃ ግዢ አስተዳደር ቡድን በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በጨረታው ላይ ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ይጠበቅባችኋል:: 

  • ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ ቫት ሰርተፍኬትና ያለፈው ወር ቫት ሪፖርት የተደረገበት ማስረጃ የንግድ ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት:: 
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በእያንዳንዱ ጨረታ ዶኩሜንት ላይ የተገለፀው መጠን በቢሯችን ስም በሲፒኦ አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል። 
  • ቢሯችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% በመቶ ለመቀነስ ወይም ለመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  • ጨረታው ሰኔ 06 ቀን 2011 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓትላይ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሯችን የዕቃ ግዢ አስተዳደር ቡድኑ ይከፈታል። 
  • ቢሯችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች፡0344403663/ 0344404346 ወይም በፋክስ  ቁጥር 0344409971 መጠየቅ ይቻላል። 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ