የመቐለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት ጽህፈት ቤት

ጨረታ ዝወፀሉ ዕለት 2/ 13 /2010 ዓም 

1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው 

2. ደረጃ 7 /ሰባት/ እና ከዛ በላይ ፍቃድ ያላቸው

3. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲከለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ 

4. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት 200 /ሁለት መቶ/ በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ። 

5. ጨረታ ዶክሜንቱን ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2011ዓ.ም 9:00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።

6. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 

7. ሁሉም ተጫራቾች ብር 50,000 /ሃምሳ ሺ/ የጨረታ ማስከበሪያ በCPO፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል

8. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው። 

9. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፕስፊኬሽን ውጪ ተቀባይነት የለውም። 

10. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ5ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ጥልቅ ውሃ ጉድጓዱን ቆፍሮ ማስረከብ የሚችል 11. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ 

12. ጨረታ ሣጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም። 

13. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው። 

14. ጽ/ቤቱ ጨረታውን እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 15. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት o

15.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም o

15.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል። ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተበጠቀ ነው።