ለዕቃዎችና ተያያዥ አገልግሎቶች ግዥ የሚውል
የፕሮፎርማ ጨረታ ሰነድ (RFQ)
የሚገዛው ዕቃ/ተያያዥ አገልግሎት:- home solar light
የግዥው መለያ ቁጥር:- ET-TIGRAY-FSRP-515718-GO-REQ
የፕሮጀክቱ ስም:- የትግራይ ምግብ ስርዓት ማጠናከርያ ፕሮግራም/ FSRP የግዢው ዘዴ/ግዢው የሚከናወንበት መንገድ/:- የፕሮፎርማ ጨረታ
የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀበት ቀን:-12/06/2018 ዓ.ም
ቁጥር 2173/1440-79
ቀን 12/06/18
የጥቅል ሰነድ ቁጥር: ET-TIGRAY-FSRP-515718-GO-RFQ
የትግራይ ክልል ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/ FSRP የበጀት ድጋፍ የተለያዩ home solar light ግዥ ለማካሄድ ስለሚፈልግ ከዚህ የጨረታ ደብዳቤ ጋር አባሪ ተደርጎ በተያያዘው ዝርዝር መሰረት ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ እንዲያቀርቡለት ይጋብዛል፡፡
በዚህ የመጫረቻ ዋጋ መጠየቂያ ሰነድ ውስጥ ካልተሻሻለ በቀር ማንኛውም ትዕዛዝ የሚፈፀመዉ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ለአካባቢ ግዥዎች ባወጣው "አጠቃላይ የዉል ሁኔታዎች" ይዘት መሰረት ይሆናል፡፡
ተጫራቾች ይህን የመጫረቻ ሰነድ ከክፍል-ሀ ጀምሮ እስከ ክፍል-ሐ ድረስ በጥንቃቄ አንብበው በመረዳት ዋጋቸውን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ክፍል ሀ፦ ቢሮው የሚፈልጋቸው መስፈርቶች
1. ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ ጥራታቸውን የጠበቁ home solar light ግዥ ሲሆን ዕቃው የሚቀርብበት (የሚረከብበት) ቦታ ከስፔስፊኬሽኑ ጋር ተያይዞ ይገኛል፡፡
2. ግዥው እንዲቀርብ የሚፈለግበት ጊዜ የውል ስምምነት ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ በ 15 ቀናት ውስጥ ይሆናል፡፡
3. የሚቀርበው የመጫረቻ ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ይህ የግዥ ግብዣ ደብዳቤ በእጅ ከደረሰ ዕለት ጀምሮ ለ 30 ቀናት ይሆናል፡፡
4. ለግዥው የሚሰጠው ዋስትና ግዜ የሚቆይ መሆን አለበት፡፡ አይመለከተዉም (NA)
5. የመጫረቻ ዋጋና ደጋፊ ሰነዶች በክፍል "ለ" ውስጥ በተጠቀሱ ግዴታዎች መሰረት መሆኑን ማመልከት ይገባቸዋል፡፡
6. የተሞላውን የመጫረቻ ዋጋ (ፕሪፎርማ) በታሸገ ፖስታ በማድረግ እስከ 18/06/2018ዓ/ም ሰዓት ከጠዋቱ 3፡30 ድረስ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
7. የፕሮፎርማው ጨረታ የሚከፈትበት ቀን 18/06/2018ዓ/ም ሰዓት ከጠዋቱ 4፡00 ይሆናል፡፡
8. ማንኛውም ተጫራች ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በፊት የዋጋ ማቅረቢያው ሰነዱ/ የመወዳደሪያ ሃሳብ/ ማስገባት ይኖርበታል፡፡ ጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በኋላ የቀረበ
የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ የመወዳደሪያ ሃሳብ ተቀባይነት የለውም፡፡
9. የመወዳደሪያ ሃሳቡ ዋጋ የሚቀርበው በኢትዮጵያ ብር ብቻ ይሆናል፡፡
10. ተጫራቾች የተሞላውን የመጫረቻ ዋጋ (ፕሪፎርማ) ለፕሮግራሙ ከፍተኛ የግዢ ባለሙያ ቢሮ ቁጥር 12 ማቅረብ (ማስረከብ) አለባቸው፡፡
11. አቅራቢዎች ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥርና በፊደል መፃፍ አለባቸው፡፡ በቁጥርና በፊደል በተገለፀው የዋጋ መጠን መካከል _ አለመጣጣም _ ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡ በነጠላ ዋጋ እና በጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡
12. አቅራቢዎች በእያንዳንዱ የዕቃ ዝርዝር ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ውስጥ የዕቃውን ዓይነትና ብዛት፣ ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋውን መሙላት እንዲሁም ቀን፤ ፊርማና የድርጅቱን ማህተም ማስፈር ይገባቸዋል፡፡
13. ለአሸናፊ ተጫራች ዕቃውን ሙሉ ለሙሉ በውሉ መሰረት አጠናቆ ማስገባቱንና ማጠናቀቀን ከተረጋገጠ በኋላ ቢበዛ በ5 አምት ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል፡፡
14. የመወዳደሪያ ሃሳብ ማቅረቢያ ቋንቋው አማርኛ ነው፡፡
15. ተጫራቶች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን ያካትት መሆነን ተረድተው የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
16. የጨረታ ማወዳደሪያው በሚከተለው መሰረት ይሆናል
16.1. የቀረቡት ዕቃዎች ቴክኒካል መስፈርቶቹን ያሟሉ መሆናቸውን ይረጋገጣል፡፡
16.2. በቀረበው ዋጋ ላይ የሂሳብ ድምር ስህተት ካለ እንዲታረም ይደረጋል፡፡ ውድድሩ የሚካሄደው እና ዝቅተኛ ዋጋ አቅራቢው የሚለየው በታረመው ዋጋ መሰረት ይሆናል፡፡