የሃራጅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 9/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እንዲሁም በስሩ በሚገኙት የመቆጣጠሪያ እና መቅ/ጣቢያዎች መጋዝን ውስጥ የሚገኙትን የተለያዩ እቃዎች ማለትም ለመጀ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች ለሁለተኛ ግዜ ጨረታ የወጡ የንፅህና ዕቃዎችና ልዩ ዕቃዎች እንዲሁም ለሶስተኛ ግዜ ጨረታ የወጡ የግብርና ግብኣቶች፤የመኪና መለዋወጫዎችና የኤሌክትርክ ዕቃዎች በሃራጅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን ስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መሳተፍ ይችላል፡፡
1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ የምችሉ፡
2. ተጫራቾች በጨረታው ለመመዝገብ ሲመሰ ከላይ በተ.ቁ 1 የተገለፁት ሰነዶች ኦርጅናል እና ኮፒ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3. ከላይ በተ.ቁ 1 በተገለፀው ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ቢኖርም ግምታዊ ዋጋቸው ከብር 500,000 በታች የሆነ ማንኛውም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት እንዲያቀርብ አይገደድም፡፡
4. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000012078537 ገቢ በማድረግ የባንክ አድቫይሱን በመያዝ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመሄድ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመሄድ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከጥር 29/05/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥር 07/06/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ድረስ የተጠቀሱት ማስረጃዎች ኮፒ በማቅረብ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል።
5. በሃራጅ ጨረታው ለመሳተፍ ተጫራቾች ለኮንስትራክሽን ዕቃዎች ብር 30,000 ለንፅህና ዕቃዎች 105,000 ለልዪ ልዪ ዕቃዎች ብር 2,000 ለግብርና ግብአቶች ብር 12,600 ለመኪና መለዋወጫዎች ብር 30,000 እና ለኤልክትርክ ዕቃዎች ብር 300,000 ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ (CP.O) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መንእዶ : የኢትዮጵያ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ።
6. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
| የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንገረሉ ዓይነት | ጨረታው ዓይነት | የንብረት መስክ ቀን የጨረታ ሰነድ ከዱ ቀን ጀምሮ | የጨረታ ሰሚያ እና ፈቻ ቀንና ሰዓት | |
|---|---|---|---|---|---|
| ከ | እስከ | ||||
| መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት | የተለያዩ እቃዎች | ሃራጅ ጨረታ | 29/05/2018 | 07/06/17 | 07/06/2018 ከቀኑ 7፡30 ጨረታው ይጀመራል። |
6. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት ሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
7. ለጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
8. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ስለ ማሸነፋቸው ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉት የዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
9. ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡
10. በጨረታ የሚሸጠው ዕቃ በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፣ ወኪል ፣ ባለቤት ወይም ቤተሰብ የነበረ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ ኣይችልም፡፡ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን፡፡