የኢትዮጵያ ልማት ባንክ

ጥር 18/2018 ዓ/ም

የመጋዘን ኪራይ የጨረታ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ማሽነሪዎች ለማስቀመጥ የሚያገለግል መጋዘን በጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታዉ መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በሟሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ፡፡

1. አጠቃላይ የመሬት ይዞታው ከ2,000 ሜካ ያላነሰ ሆኖ የሼዱ ይዞታ ከ1,000 ሜካ ያላነሰ መሆን ይኖርበታል፤

2. የአጥሩ መሰረት በሰሜንት አርማትራ (Grade beam) የተሰራ ሆኖ ቁመቱ ቢያንስ 25 ሜትር የሆነ፤

3. የሼዱ ወለል ቢያንስ በሰሜንት አርማርታ የተሞላ፤

4. የሼዱ በር ቁመትና ጎን ቢያንስ 44 ሜትር የሆነ፤ 5 የኤሌክትሪክ መብራት ያለው፤

6. የእሳት አደጋ መከላከያ መሳርያዎች ያለው፤

7. ቢያንስ አንደኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ያለው

8. የዓመቱ በዘርፉ (በኪራይ እና ኣከራይ) ህጋዊና የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማስረጃዎች ማቅረብ ሚችሉ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ወይም ቲኦቲ ተመዝጋቢ የሆኑ፤

9. በጨረታ ሰነዱ ላይ የተሰረዘ እና የተደለዘ ሆኖ ለመለየት የሚያስቸግር ከሆነ ተቀባይነት የለዉም፤

10. ዲስትሪክቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፤

11. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ስም እና አድራሻቸውን በመጥቀስ ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በማያያዝ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ምድር ቤት ላይ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 11:00 ድረስ ብቻ ማስገባት የሚቻል ሆኖ ጨረታው ጥር 25 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 3:00 ላይ የሚከፈት ይሆናል።

የኢትዮጵያልማትባንክ መቐለቅርንጫፍ ስልክቁጥር 0344410233 ፖ.ሳ.ቁ.474