መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ.የግል ማህበር (SWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተገለፀ የPreengineering Building (PB) ኣካል የሆነ ንብረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ድርጅታችን ይጋብዛል::

በጨረታ የሚገዙ ግብኣቶች ዝርዝር

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝርመለኪታ ብዛትማብራርያ
01PPG steel Sheet Blue 1000 x 0.5mmTonከለርበናሙና መሰረት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2018 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የህዳር ወር ቫት ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የህዳር ወር ቫት ማሳወቅያ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ሰነድ እና የሚመለስ ኦርጅናል በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ 13/01/2026 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 27/01/2026 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት የማይመለስ 200 ብር (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል እና ለናሙና የቀረበ ንብረት በማየት የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ተጫራቶች የተሟላ የጨረታ ሰነድ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀሚሮ እስከ 27/01/2026 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ማስገባት ኣለባችው::

4. ጨረታው በ27/01/2026 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና በግልፅ መጥቀስ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

አለመሆኑን

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው · ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::

7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በኋላ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨ

ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ 20 ( ሃያ) ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም፤ እንዲሁም በቅድመ ሁኔታ የተመሰረተ ዋጋ ተቀባይነት የለውም፤ በተጨማሪም ስርዝ ድልዝ እና የተጫራቶች የስልት ስህተት ያለበት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ በ7 ቀናት ውስጥ የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::

መስፍን ብረታብረት እና ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር

ስልክ-+251914729699/+251914708567

አዲስ-አበባ

ስልክ-+251-914726541 መደወል ይችላሉ