መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ.የግል ማህበር (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተገለፁትን የተለያዪ መጠን ያላቸው የፋብሪካ ግብኣቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ድርጅታችን ይጋብዛል::

በጨረታ የሚገዙ ግብኣቶች ዝርዝር

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝርመለኪታ ብዛትማብራርያ
01Welding Wire 1.2mmRoll4001 Roll 15kg
02Steel Cable Ø12mmM6300
03Self Screw Drill 5.5*55mmPcs12,226
04Nut with Washer Gal, M24 *3Pcs2,300
05Washer, Galvanized M20Pcs450
06Paint, White EurotruckerLiter2,600
07Paint,antirust GrayLiter600
08Paint,blush Green acc. RAL 5021Liter600Trans Eth, Color
09Thinner UN 1263Liter2,400
10Chain Ø13mm,L=7000mmPcs82

የጨረታው መስፈርት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2018 ዓ/ም የ o የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የህዳር ወር ቫት ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር(ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የህዳር ወር ቫት ማሳወቅያ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ሰነድ እና የሚመለስ ኦርጅናል በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ 07/01/2026 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 21/01/2026 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት የማይመለስ 200 ብር(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል እና ለናሙና የቀረበ ንብረት በማየት የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ተጫራቶች የተሟላ የጨረታ ሰነድ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀሚሮ እስከ 21/01/2026 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ማስገባት ኣለባችው::

4. ጨረታው በ21/01/2026 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መጥቀስ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::

7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በኋላ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ (ኣስራ ) ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም፤ እንዲሁም በቅድመ ሁኔታ የተመሰረተ ዋጋ ተቀባይነት የለውም፤ በተጨማሪም ስርዝ ድልዝ እና የተጫራቶች የስልት ስህተት ያለበት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ በ7 ቀናት ውስጥ የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::

ለበለጠ መረጃ

መስፍን ብረታብረት እና ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር

ስልክ-+251-914726541 መደወል ይችላሉ