የግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 7/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመጋዝን የሚገኙትን እቃዎች ማለትም የምግብ ምርቶች የመጠጥ ምርቶች፤የህእል ዕቃዎች የኤሌትርክ ዕቃዎች የመለክያ መሳርያዎች እንዲሁም ሌሎች ልዩ ልዩ እቃዎች በጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መሳተፍ ይችላል፡፡
1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ሰረቲፊኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ የሚችል፡፡
2. ከላይ በተ.ቁ 1 የተገለፀው ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ቢኖርም ግምታዊ ዋጋቸው ከብር 500,000 በታች የሆነ ማንኛውም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት እንዲያቀርብ አይገደድም፡፡
3. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/በመክፈል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉምሩከ ኮሚሽን መቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000012078537 ገቢ በማድረግ የባንክ አድቫይሱን በመያዝ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመሄድ የመ/ቤቱ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመሄድ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከታሕሳስ 06/2018 ዓም ጀምሮ እስከ ታሕሳስ 14/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ድረስ የተጠቀሱት ማስረጃዎች ኮፒ በማቅረብ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል፡፡
4. በግልፅ ጨረታው ለመሳተፍ ተጫራቾች ዕቃው ለመግዛት የሚያቀርቡትን የመጫረቻ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ (CPO) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ::
5. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
| የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንገረሉ ዓይነት | ጨረታው ዓይነት | የንብረት መስክ ቀን የጨረታ ሰነድ ከዱ ቀን ጀምሮ | የጨረታ ሰሚያ እና ፈቻ ቀንና ሰዓት | |
|---|---|---|---|---|---|
| ከ | እስከ | ||||
| የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት ጉምሩክ ኮሚሽን | የተለያዩ እቃዎች | ግልፅ ጨረታ | 06/04/2018 | 14/04/201 | 14/04/2018 ከቀኑ 6:00 ተዘግቶ በዚያውኑ ቀን 8፡00 ጨረታው ይጀመራል። |
5. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
6. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤ ሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
7. በጨረታ ተወዳድረው ለተሸነፉ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
8. የጨረታው አሸናፊ ጨረታወ ቀናት ውስጥ ያሸነፉት ቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ስለ ማሸነፋቸው ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
9. ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡
10. በጨረታ የሚሸጠው ዕቃ በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፣ ወኪል ፣ ባለቤት ወይም ቤተሰብ የነበረ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም፡፡
11. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡
12.ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን፡፡