Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

ለ3 ጊዜ የዘር መጋዘን ኪራይ ጨረታ

ከላይ በርእሱ እንተጠቀሰዉ በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ ምርጥ ዘር አቅቅርቦት ለዘር ማከማቻ የሚሆን መጋዘን ለሶስት ወራት ሆኖ እንደየሁኔታዉ እየታየ የሚታደስ ዉል በማስገባት ለመከራየት ስለሚፈልግ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ባለመጋዘኖች መወዳደር የምትችሉ መሆናችሁ እንገልፃለን።

1. የታደሰ የዘመኑ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል

2. የቫት ተመዝጋቢ የሆነ

3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያለዉ

4. ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ መቅረብ

5. ዉኃ፣መብራት፣ጥበቃ የሚያሟላ በራሱ ወጪ የሚሸፍን

6. ስፋቱ ወደ 1000 አከባቢ የሆነ

7. የዘር ማበጠርያ ማሽን የጫነች መኪ

8. ወለሉ ንፁህ እና ልሙጥ ስሚንቶ የሆነ

9. በቂ መስኮት እና በሮች ያሉት

10. ቆርቆሮዉ ዉሃ የማያስገባ ማስገባት የሚችል ቢያንስ 4ሜትር ከፍታ በር ያለዉ

11. ከባድ መኪና ማስገብያ ግቢ ያለዉ(የክረምትና የበጋ)

ከላይ የተዘረዘሩትን የምታሟሉ ተጫራቶች ከ 06/4/2018 ዓ/ም እስከ 09/4/2018ዓ/ም በስራ ስዓት ወደ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በመምጣት የዋጋ ማቅረብያዉ ሰነድ ወስዳቹ ዋጋዉ ተሞልቶ በፖስታ ታሽጎ ወደ ጨረታ ሳጥን አስከ 09/04/2018 ዓ/ም 8፡00 ስዓት የጨረታ ሰነዱን እንድታስገቡ እየጋበዝን ጨረታው 711004 09/04/2018 ዓ.ም ከጥዋት 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 8፡15 ሰዓት በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይከፈታል፡ ስለዚህ የኪራዩ አፈጻጸሙ በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን እንገልፃለን፣ ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ ማብራሪያ በሚቀጥለው አድራሻ መጠቀም ይቻላል።

አድራሻ

ሓሚዳይ ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ ፊት

መቐለ

ስ ቁጥር 0914724990