Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

ለ2 ጊዜ መጋዘን ኪራይ ጨረታ ማስታወቅያ

ከላይ በርእሱ እንተጠቀሰዉ በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ ምርጥ ዘር አቅቅርቦት ለዘር ማከማቻ የሚሆን መጋዘን ለሶስት ወራት ሆኖ እንደየሁኔታዉ እየታየ የሚታደስ ዉል በማስገባት ለመከራየት ስለሚፈልግ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ባለመጋዘኖች መወዳደር የምትችሉ መሆናችሁ እንገልፃለ

1. የታደሰ የዘመኑ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል

2. የቫት ተመዝጋቢ የሆነ

3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያለዉ

4. ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ መቅረብ አለበት

5. ዉኃ፣መብራት፣ጥበቃ የሚያሟላ በራሱ ወጪ

6. ስፋቱ ወደ 1000 አከባቢ የሆነ

7. የዘር ማበጠርያ ማሽን የጫነች መኪና ባት የሚችል ቢያንስ 4ሜትር ከፍታ በር ያለዉ

8. ወለሉ ንፁህ እና ልሙጥ ስሚንቶ

9. በቂ መስኮት እና በሮች ያሉት

10. ቆርቆሮዉ ዉሃ የማያስገባ

11. ከባድ መኪና ማስገብያ ግቢ ያለዉ(የክረምትና የበጋ)

12. ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ቅርብ የሆነ

ከላይ የተዘረዘሩትን የምታሟሉ ተጫራቶች ከ 29/3/2018 ዓ/ም እስከ 03/4/2018 ዓ/ም በስራ ስዓት ወደ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በመምጣት የዋጋ ማቅረብያዉ ሰነድ ወስዳቹ ዋጋዉ ተሞልቶ በፖስታ ታሽጎ ወደ ጨረታ ሳጥን አስከ 03/04/2018 ዓ/ም 4፡00 ስዓት የጨረታ ሰነዱን እንድታስገቡ እየጋበዝን ጨረታው 03/04/2018 ዓ.ም ከጥዋት 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4፡15 ሰዓት በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ ስለዚህ የኪራዩ አፈጻጸሙ በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን እንገልፃለን፣ ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው" ለተጨማሪ ማብራሪያ በሚቀጥለው አድራሻ መጠቀም ይቻላል፡፡

አድራሻ

ሓሚዳይ ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ ፊት ለፊት

መቐለ ስ/ቁጥር 0914724990