መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ.የግል ማህበር (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተገለፁትን የተለያዪ መጠን ያላቸው የፋብሪካ ግብኣቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ድርጅታችን ይጋብዛል::

በጨረታ የሚገዙ ግብኣቶች ዝርዝር

Lot-01

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝር>መለኪያብዛትማብራርያ
01Sheet Metal 2500*1000*2mm, st-37Pcs592
02Sheet Metal 2500*1250*2mm,st-37Pcs105
03Pipe,Bronze Ext 056*int035*110mmPcs66
04Round Rod,steel Ø30*6000mm,st-37Pcs09
05Round Rod,steel 025*6000mm,st-37Pcs02
06Round Rod,steel 20*6000mm st-37Pcs75

Lot-02

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝር>መለኪያብዛትማብራርያ
01Brake System for 3-Axle draw barSet06
02Deep stick,3Meter length widthPcs32
03Steel Cable Ø12mmM4,000
04Steel Cable 8*8mmM156
05Silicon SealantPcs115
06Wire, Steel welding 04mm for submerged arc weldingRoll1201 Roll 25kg
07Welding Wire 1.2mmRoll2211 Roll 15kg
08Elbow PVC 110mm, 45 degreePcs227
09Self Screw Drill 5.5 * 55mmPcs12,226

የጨረታው መስፈርት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2018 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር

ከፋይ መለያ ቁጥር እና የጥቅምት ወር ቫት ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የጥቅምት ወር ሻት ማሳወቅያ

የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ሰነድ እና የሚመለስ ኦርጅናል በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ 04/12/2025 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 18/12/2025 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት የማይመለስ 200 ብር(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል እና ለናሙና የቀረበ ንብረት በማየት የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ተጫራቶች የተሟላ የጨረታ ሰነድ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀሚሮ እስከ 18/12/2025 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ማስገባት ኣለባችው::

4. ጨረታው በ18/12/2025 እ.ኤ.አ ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጥቀስ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ለ lot -01 ብር 150,000.00 (ኣንድ መቶ ኣምሳ ሺህ ብር) እንዲሁም ለ lot -02 ብር 100,000.00 (ኣንድ መቶ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::

7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በኋላ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሽንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ 5 (ኣስራ ኣምስት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም፤ እንዲሁም በቅድመ ሁኔታ የተመሰረተ ዋጋ ተቀባይነት የለውም፤ በተጨማሪም ስርዝ ድልዝ እና የተጫራቶች የስልት ስህተት ያለበት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ በ7 ቀናት ውስጥ የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::