የመቐለ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት

የጨረታ ማስታወቅያ

የመቀሌ ከተማ እቅድና ፋይናንስ ፅ/ቤት በመቀለ ከተማ ክ/ከተማ ኲሓ ሎት 1 እና በክ/ከተማ ዓይደር ሎት 2 የሼድ ግንባታ ስራ በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል ። ስለዚህ በዚ ጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ከታች የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታማሉ ተወዳዳሪዎች ጨረታ ሰነድ ከፅ/ቤታችን በመውሰድ እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

ተፈላጊ መስፈርቶች

1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የሻት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የቅርብ ወር ቫት ሪፖርት፣ በኮንስትራክሽን ስራ ደረጃ 7 BC እና ከዛ በላይ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ ።

2. የጨረታ ማስከበርያ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 150,000.00 (ኣንድ መቶ ኣምሳ ሺ ብር ብቻ ) በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO)፣ በጥረ-ገንዘብ ወይም በሁኔታ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በፅህፈትቤታችን

ስም ማስያዝ የሚችሉ ።

3. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ሰኣት የማይመለስ ብር 500.00(ኣምስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ ።

4. ተጫራቾች የፋይናንሻል የጨረታ ሰነዳቸው ኣንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ።

5. ጨረታ ከ 03/02/2018 ዓ/ም እስከ 15/03/2018 ዓ/ም 3:30 ለተጫራቾች ክፍት ሁኖ የሚቆይ ሲሆን በዚህ ቀን 4:00 ተዘግቶ 4:30 ሰዓት ይከፈታል ።

6. ጨረታ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰ ቀን በፅ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 033

ይከፈታል።

7. ተጨራቾች በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ገፅ የድርጅት ማህተም እና ፊርማ ማድረግ ኣለባቸው ።

8. በጨረታዉ መሳተፈ የሚችሉት በግንባታ ስራዉ ቢያንስ ኣንድ እና ከዚያ በላይ ተመሳሳይ ስራ የሰሩ

መሆን ኣለባቸዉ፡፡

9. ፅህፈት ቤታችን ጨረታ ከተከፈተ በኋላ 20% የመጨመር እና የመቀነስ መብት ኣለው ።

10. ፅህፈት ቤታችን የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታ በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

11. ኣድራሻችን በመቐለ ከተማ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ ቢሮ ቁጥር 033 ይገኛል።

12. ለበለጠ ማብራርያ በስራ ሰኣት በኣካል ቀርባችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ ።