የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 01/ 2018 ዓ/ም
ፖም ጎልድ ፍሩትስ ሓላ/የተ/የግ/ማሕበር ከአሪድ ዩኒቨርሲቲ /እንዳየሱስ ካምፓስ/ ፊት ለፊት የሚገኝ ዘመናዊ የወይንና ፍራፍሬ የእርሻ ኢንቨስትመንት ሲሆን በግቢው ውስጥ የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት/ለማስቆፈር/ ስለፈለገ የሚከተሉት መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ይጋብዛል።
1. በዘረፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር IIN ያላቸው፡፡
3. .ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲከለር ያደረገበት ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ
4. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ወደ ድርጅታችን በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 2 መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች 200,000/ሁለት መቶ ሺ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በCPO ብቻ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል
6. . ጨረታው ከቀን 21/01/2018ዓ/ም እስከ 30/01/2018 ዓ/ም ክፍት ሁኖ ቆይቶ በ01/02/2018ዓ/ም ጧት 3:30 ሰዓት ተዘግቶ (4:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
7. ተጫራቾች ዝርዝር የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ መግለጫ/Specification/ ከጨረታ ሰነዱ ማየት ይችላሉ።
8. ተጫራቾች የጨረታ ዶክሜንቱን ኦርጅናልና ኮፒ በማለት በሁለት በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው
9. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለባቸው በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
10. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፕስፊኬሽን ውጪ ተቀባይነት የለውም።
11. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ 10% በCPO ማስያዝ የሚችልና በ5ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ጥልቅ ውሃ ጉድጓዱን ቆፍሮ ማስረከብ የሚችል
12. ጨረታ ሣጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም።
13. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ተከታታይ ቀናት ነው።
14. ድርጅታችን ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተበጠቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0914314808 ወይም 0935231253 መደወል ይችላሉ።