የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ERMMB/NCB/004/2018 E.C

የኢ/ያ ገቢዎች ሚኒስቴር መቐለ ቅ/ፅ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተሉትን አገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል::

1. የሰራተኞች የመኪና ሰርቪስ እና የሙሉ ቀን የመኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

  1. ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ማለትም የ2017 ዓ/ም ወይም 2018 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
  2. የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ
  3. 15 ሰው የመጫን አቅም ያለው ሚኒባስ ወይም ተመሳሳይ ተሽከርካሪ ማቅረብ የሚችሉ
  4. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  5. ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይጠበቅቸዋል።
  6. የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ ብር 100,000.00(አንድ መቶ ሺህ)በባንክ በተመሰረተ ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ሶስት(3) ቀን እስኪቀር ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ አጠገብ የሚገኘው የትግራይ አካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ፅ/ቤቱ የግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ የቤት ቁጥር 20 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
  8. የጨረታ ሰነድ መሸጫ የሚያበቃው መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ተጫራች እንዲያውቁት ያስፈልጋል።
  9. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ ዕለት ልክ 4:30 በመስሪያ ቤቱ የመሰብሰብያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል።
  10. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል።
  11. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  12. ተጫራቾች ሁሉም ቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
  13. ተጫራቾች የምታቀርቡት የሰራተኛ የሰርቪስ ተሽከርካሪዎች ጥራታቸው የጠበቁ እና ምርት ዘመን ሞዴል 2007 እና ከዛ በላይ መሆን ይኖርባቸዋል።
  14. ተጫራቾች የምታቀርቡት የሙሉ ቀን የመኪና ኪራይ አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ጥራታቸው የጠበቁ እና የምርት ዘመን ሞዴል ለሚኒባስ ወይም ተመሳሳይ ተሽከርካሪ 2007 እና ከዛ በላይ መሆን ይኖርባቸዋል።
  15. የመጫን ዓቅም በሊብሬ መሰረት እና በአካል የሚረጋገጥ መሆኑን።
  16. የሚያቀርቡት ሚኒባስ ወይም ተመሳሳይ ተሽከርካሪ በሊብሬ 5 ሰው የመጫን አቅም ያለው መሆኑን፡
  17. ተጫራቾች ሚኒባስ ወይም ተመሳሳይ ተሽከርካሪ ደረጃ ጥራት ማቅረብ የሚችል።

ስልክ ቁጥር 0934345898/0935282274/ ፋክስ 0344407309

በኢ/ያ ገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት