አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/1990 እና 216/1992 እንዲሁም በአዋጅ ቁጥር 1147/2012 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት በሰንጠረዡ ላይ የተዘረዘሩትን ንብረት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ተ.ቁ

የተበዳሪው ስም

የንብረት አስያዥ ስም

አበዳሪ

ቅርንጫፍ

የንብረቱ አድራሻ

የቦታው ስፋት (ካ/ሜ)

የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት

የንብረቱ አይነት

የጨረታ መነሻዋጋ

ጨረታው የሚከናወንበት ቦታ፣ ቀን እና ሰዓት

ከተማ

ክ/ከተማ

ቀበሌ

ቤ.ቁ

1

አንድል ንግድና ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

አንድል ንግድና ንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ቦሌ መድኃኔ ዓለም

መቐለ

ሓድነት

ስምረት

--

401.30ካ.ሜ

71042/05/9764

B+G+4 በግንባታ ላይ ያለ የንግድ ሕንፃ

42,598,670.08

ጨረታው የሚከናወነው በመቐለ ከተማ በሚገኘው በባንኩ ሰሜን ሪጅን ጽ/ቤት መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 ድረስ ይሆናል፡፡

ማሳሰቢያ፡-

  1. ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) ወይም 25% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (CPO) ብቻ በአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ/ማ ስም በማሠራትና ለጨረታ ማስከበሪያነት በማስያዝ መጫረት ይችላሉ።
  2. ጨረታው የሚካሄደው ንብረቱ በሚገኝበት መቐለ ከተማ ባለው በባንኩ ሰሜን ሪጅን ጽ/ቤትይሆናል፡፡
  3. የተጫራቾች ምዝገባ የሚከናወነው በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ 4:00-5:30 ድረስ ይሆናል። ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለንብረቱ የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ሲሆን የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለዮ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው የሚቀጥል ይሆናል።
  4. በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ከሚያካሂደው የባንኩ የህግ አገልግሎት መምሪያ ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
  5. የጨረታው አሸናፊ ቀሪውን ገንዘብ አሽናፊነቱ በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በአስራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ በሲ.ፒ.ኦ (CPO) ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል። በጨረታው የተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ይመለስላቸዋል።
  6. የጨረታው አሸናፊ ካሸነፈበት ዋጋ ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ተጨማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ ይከፍላል፡፡
  7. ለጨረታ የቀረቡትን ንብረቱ ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ ከ7 (ሰባት) የሥራ ቀናት አስቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል፡፡
  8. በሐራጅ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም የነዚህ ሕጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው፡፡ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታውን ሂደት ለመከታተል በተጠቀሰው ቦታ እና ሰዓት እንድትገኙ እያሳሰብን ካልተገኛችሁ በሌላችሁበት ጨረታው የሚከናወን መሆኑን እንገልፃለን።
  9. ባንካችን ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
  10. ከሚሸጠው ንብረት ጋር የተያያዙ ከጨረታው በፊትም ሆነ በኋላ ማንኛውም ለመንግስት ሊከፈሉ የሚገባቸው ያልተከፈለ ውዝፍ የሊዝ እዳ፣ ወጭዎች፣ ግብር እና የሊዝ ክፍያ እንዲሁም በንብረት ማስተላለፍ ሂደት የሚመጡ ማንኛውም አይነት ክፍያዎች ወይም ግብር ሙሉ በሙሉ የጨረታ አሸናፊው ገዥው / የሚሸፍን ይሆናል፡፡
  11. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ኢማ ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት መምሪያ በስልክ ቁጥር 011-662-7120 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ