የጨረታ ማስታወቂያ
በአፈ/ከሳሶች እነ ጌቱ ኪሮስ 178 ቁ.ሰዎች እና በአፈ/ተከሳሾች እነ አቶ ገ/ሄር ካሕሳይ 3 ቁ/ሰዎች በመካከላቸው ባለው የአፈጻጸም ክርክር ንብረትነቱ የአፈ ተከሳሽ አቶ ገ/ሄር ካሕሳይ የሆነ በመቐለ ከተማ፣ ቀ/ወያነ ክ/ከተማ የሚገኝ ስፋቱ 233 ካ.ሜ. የሆነ ቤትና ቦታ አዋሳኙ በምስራቅ ብርሃን ተሰማ፣ በምዕራብ- ብርሃን ክፍለ፣ በሰሜን-ግደይ ሓዱሽ፣ በደቡብ-መንገድ የሚዋሰን በ 1,903,579.15 (አንድ ሚልዮን ዘጠኝ መቶ ሶስት ሺ አምስት መቶ ሰባ ዘጠኝ ብር ከ 15/100) መነሻ ዋጋ በግልጽ ጨረታ እንዲሸጥ ፍርድ ቤቱ ስላዘዘ መጫረት የምትፈልጉ ለ ቀን 19/01/2018 ዓ/ም ከጠዋት 3፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ በግልጽ ጨረታ ስለሚሸጥ በቀኑና ቦታው ተገኝታችሁ እንድትጫረቱ የጨረታ ውጤት ደሞ ለቀን 22/01/2018 ዓ/ም 3፡30 ሰአት እንዲቀርብ የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍታሓብሄር ችሎት ኣዟል።
የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት