ያገለገሉ ልዩ ልዩ ንብረቶች ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ትግራይ ቅርንጫፍ ያገለገሉ ልዩ ልዩ ንብረቶች ማለት ፣ ፕሪንተር ፣ ዩፒኤስ ወንበሮች ላፕቶፕ ኮምፒተሮች ኤልሲዲ ሞኒቶር እና ዶክ ስቴሽን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር
1. በጨረታው የሚወዳደሩት ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ሠነድ ለመግዛት ሲመጡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ ወይም የታደሰ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ትግራይ ቅርንጫፍ ሁለተኛ ፎቅ ንብረት ክፍል በመምጣት የንብረቶችን ዝርዝር መረጃ የያዘ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ ከፍለው መውሰድ ይችላሉ፣
3. ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹን ከላይ በተጠቀሰው መ/ቤት በመሄድ መመልከት ይችላሉ፣
4. ተጫራቾች ብር 1000.00 (ኣንድ ሺ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
5. የጨረታው መገምገሚያ መስፈርት ዋጋና የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ሲፒኦ) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ነው፡፡ እነዚህን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል ማለት ነው፡፡
6. የጨረታው በቀን 18/8/2025 ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ትግራይ ቅርንጫፍ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መክፈት አያስተጓጉልም፣
8. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ የጠቅላላ ዋጋው 10 ፐርሰንት የውል ማስከበርያ በማስያዝ ውል ማሰር ኣለባቸው
9. ትወዳዳሪዎች በጨረታ ሂደቱ ቅሬታ ካለባቸው በ5 ተከታታይ ቀናት ቅሬታቸው በፅሁፍ ማቅረብ ይችላሉ
10. ንብረቶቹን ውል ከታሰረበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ማንሳት ይኖርባቸዋል፡፡
11. በዚህ ቀነ ገደብ ንብረቶቹን ካልተነሱ ግን በየቀኑ 500.00 ቅጣት እየተደመረ ይሄዳል በመንግስት ንብረት ኣወጋገድ መመርያ መሰረት በመቅጣት ሁለተኛ ለወጣ ተጫራች ይሰጣል
12. ንብረቶቹን ሳይነሱ ኣንድ ወር ካለፈባቸው ደግሞ ኣስፈላጊ ቅጣቶች ውል ላሰረው ኣሸናፊ ድርጅት
13. አገልግሎቱ ያዘጋጀውን ጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከተገኘ ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
14. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር_0948061802 ወይም 0948059471ደውሎ መጠየቅ ይቻላል
15. ድርጅቱ ጨረታውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የሚችል ሲሆን በማናቸውም ጊዜ ጨረታውን ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
ኣድራሻችን፡ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ትግራይ ቅርንጫፍ ቀ/ወያነ ክ/ከተማ ፊት ለፊት ኪሮሰ ሃ/ሰላሴ ህንፃ ንብረት ክፍል ሁለተኛ ፎቅ፡፡
መቐለ