በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በፍርድ ባለሃብቶች፦
1. አቶ በሪሁ ተክላይ
2. አቶ ሰለሞን ገ/ማርያም
3. አቶ ኪሮስ ሃይሉ
የፍርድ ባለእዳ ፦ አቶ ኣብርሃም መናሶ
መካከል ባለው የአፈፃፀም ክስ የመቀለ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀን 02/11/2017 ዓ/ም በሰጠው ትእዛዝ መሰረት በፍርድ ባለእዳ አቶ ኣብርሃም መናሶ የሚታወቅ በመቀለ ከተማ ሓድነት ክ/ከተማ ጣብያ ስምረት በባለቤትነት መለያ ቁጥር 475 በሆነ ቤትና ቦታ ኣዋሳኙ በምስራቅ-477 በምዕራብ -ቲቲ473 በደቡብ-መንገድ በሰሜን- ቲቲ 474 250 ካ/ሜትር ስፋት ያለው ቤትና ቦታ በጨረታ በመነሻ ግምት ብር 15,436,706.43 /አስራ አምስት ሚልዮን አራት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ስድስት ከ 43/100/ ለፍርድ ማስፈፀሚያ እንደገና በጨረታ እንዲሸጥ ስለተፈለገ መጫረት የሚፈልግ በቀን 03/13/2017 ዓ/ም ጠዋት ከ3፡00 እስከ 6:00 ቀርቦእንዲጫረት አሸናፊ ያሸነፈበትን ገንዘብ 25% /ሃያ አምስት በመቶ/ ወዲያውኑ የሚያስይዝ መሆኑን ፣ የቀረውን ገንዘብ ደግሞ በ15 ቀን ውስጥ እንደሚከፍል፣ ስም ለማዞር የሚያስፈልገው ወጪ በጨረታ አሸናፊ የሚከፈል መሆኑን አውቆ እንዲጫረት የጨረታው ውጤት ደግሞ በዛው ቀን 03/13/2017 ዓ/ም 8:00 ሰዓት እንዲቀርብ የመቀለ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዟል።
በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመቀሌ ከተማ
ከፍተኛ ፍርድ ቤት