ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር መቐለ ቅ/ፅ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተሉትን እቃ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
-የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር: ERMMB/NCB/002/2018 E.C
የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተሉትን እቃ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
- ሎት አንድ- የፅዳት አገልግሎት ለ3ኛ ወገን(Out Source)
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
1. ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈለ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የእቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ
2. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
3. ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት
4. የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ የፅዳት አገልግሎት ለ3ኛ ወገን Out Source) ብር 50,000.00 (አምሳ ሺህ) እያንዳንዳቸው በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (C.P.O.) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ ኣጠገብ የሚገኘው የትግራይ ክልል ኣካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ ግዥ ቡድን ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 20 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ::
6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ አራተኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
7. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ CPO በማስያዝ ከመ/ቤታችን ጋር ውል ይፈራረማል።
8. መ/ቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
9. ተጫራቾች ሁሉም ቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባችኋል ተጫራቾች ዋጋው ከነቫቱ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
10. ማንኛውም ስርዝ ድልዝ ያለበት የጨረታ ስነድ ከጨረታ ውጪ ይደረጋል።
11. የጽዳት አገልግሎት ለ3ኛ ወገን(Out Source) ሙሉ specification የያዝ በጨረታ ሰነድ ላይ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ስልክ ቁጥር 034 441 1005 / 09 35 28 22 74 / 09 34 34 52 98/
ፋክስ 034 440 7309
የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር መቐለ ቅ/ጽ/ቤት