ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 1/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መጋዝን የምግብ ነክ ዕቃዎች እና የፕላስቲክ ውጤቶች በግልፅና ጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መሳተፍ ይችላል፡፡
1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ የምችሉ፡፡
2. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/በመክፈል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000012078537 ገቢ ማድረግ የባንክ አድቫይሱን በማያዝ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመሄድ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመሄድ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከሃምሌ 2/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሃምሌ 8/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 ድረስ የተጠቀሱት ማስረጃዎች ኮፒ በማቅረብ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል፡፡
3. በግልፅ ጨረታው ለመሳተፍ ተጫራቾች ዕቃው ለመግዛት የሚያቀርቡትን የመጫረቻ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ (CP.O) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ
4. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
| የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንብረቱ ዓይነት | ጨረታው ዓይነት | የንብረት መመልከቻ ቀን የጨረታ ሰነድ ከወሰዱበት ቀን ጀምሮ ሲሆን | የጨረታው የመዝጊያ እና የመከፈቻ ቀንና ሰዓት | |
|---|---|---|---|---|---|
| ከ | እስከ | ||||
| መቐለ ጉ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት | የተለያዩ እቃዎች | ግልጽ ጨረታ | 2/11/2017 | 08/11/2017 | ሃምሌ 9/2017 ዓ/ም ከቀኑ7፡30 ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ7፡45 ይከፈታል ፡ |
5. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
6. ለጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
7. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ስለ ማሸነፋቸው ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉት የዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
8. ከላይ በተ/ቁ 7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው
9. በጨረታ የሚሸጠው ዕቃ በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፣ ወኪል ፣ ባለቤት ወይም ቤተሰብ የነበረ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም፡፡
10. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ 11.ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተማሪመ
መሆኑ እንገልፃለን፡፡