መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወየግል ኩባንያ (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተፃፈው የተለያዪ የ Pre-engineering Building ግብኣቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝርመለኪያብዛትማብራርያ
01Cable Clamp O12 Class 4.6 electro Galvanizedpieces17,000በ ናሙና ሰረት
02Cable Clamp 022mm, Galvanized (as)pieces17,000በ ናሙና መሰረት
03Washer, Hill Side Aluminum M2413,000piecesበ ናሙና መሰረት
04Steel Cable O12, Length 8000mm Tensil Strength Meter (1770-2160 MPA)pieces10,000በ ናሙና መሰረት
05Stucco Per MetalKG440
06Thinner UN 1263Litre1,200
07Union PVC Ø 110mm, T=3mmpieces600
08UPVC Pipe Ø110x2.2x7000nmpieces400
09Silcon Sealant Abro 1200pieces1,200White in Colour

የጨረታ መስፈርት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ)ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ የማይመለስ እና ኦርጅናል የሚመለስ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከቀን ከ 23/06/2025 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 02/07/2025 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት መወሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ጨረታው 02/07/2025 እ.ኤ.አ ከቀኑ 8:00 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰኣት 8:30 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ዋና መስርያ ቤት በሚገኝ ላጪ FSWEI ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

4. አዲስ አበባ ለሚገኙ ተጫራቾች መቐለ ላጪ መስርያ ቤት በሚገኝ FSWE ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የጨረታ ሳንዱቅ ማስገባት ይኖርባቸዋል:

5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጠቀስ አለበት:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::

7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በ5 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ 10 ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው::ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::

ለበለጠ መረጃ
መቐለአዲስ-አበባ
ስልክ-+251914729699ስልክ-+251-914726541
ፋክስ-+251-344406225ፋክስ-+251-114709636