የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ኩባንያችን መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወየግል ኩባንያ (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተፃፈው የተለያዪ የ Pre-engineering Building ግብኣቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::
| ተ.ቁ | የዕቃው ዓይነት ዝርዝር | መለኪያ | ብዛት | ማብራርያ |
|---|---|---|---|---|
| 01 | Cable Clamp O12 Class 4.6 electro Galvanized | pieces | 17,000 | በ ናሙና ሰረት |
| 02 | Cable Clamp 022mm, Galvanized (as) | pieces | 17,000 | በ ናሙና መሰረት |
| 03 | Washer, Hill Side Aluminum M24 | 13,000 | pieces | በ ናሙና መሰረት |
| 04 | Steel Cable O12, Length 8000mm Tensil Strength Meter (1770-2160 MPA) | pieces | 10,000 | በ ናሙና መሰረት |
| 05 | Stucco Per Metal | KG | 440 | |
| 06 | Thinner UN 1263 | Litre | 1,200 | |
| 07 | Union PVC Ø 110mm, T=3mm | pieces | 600 | |
| 08 | UPVC Pipe Ø110x2.2x7000nm | pieces | 400 | |
| 09 | Silcon Sealant Abro 1200 | pieces | 1,200 | White in Colour |
የጨረታ መስፈርት
1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ)ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::
2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ የማይመለስ እና ኦርጅናል የሚመለስ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከቀን ከ 23/06/2025 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 02/07/2025 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት መወሰድ ይኖርባቸዋል::
3. ጨረታው 02/07/2025 እ.ኤ.አ ከቀኑ 8:00 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰኣት 8:30 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ዋና መስርያ ቤት በሚገኝ ላጪ FSWEI ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::
4. አዲስ አበባ ለሚገኙ ተጫራቾች መቐለ ላጪ መስርያ ቤት በሚገኝ FSWE ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የጨረታ ሳንዱቅ ማስገባት ይኖርባቸዋል:
5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጠቀስ አለበት:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::
6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::
7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በ5 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::
8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ 10 ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው::ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::
9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም::
10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::
11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል::
12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::
| ለበለጠ መረጃ | |
|---|---|
| መቐለ | አዲስ-አበባ |
| ስልክ-+251914729699 | ስልክ-+251-914726541 |
| ፋክስ-+251-344406225 | ፋክስ-+251-114709636 |