የሰሜን ሪጅን የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ህንፃ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  • ከ13 እስከ 20 ክፍል እና ከ 250 ካሬ ሜትር በላይ ሆኖ ለቢሮ አቀማመጥ እና አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ የሆነ
  • የእያንዳንዱ ክፍል ስፋት ቢያንስ 3×4m2 እና ከዚያ በላይ የሆነ
  • ቤቱ ሽንት ቤት፣ ውሃ፣ ሻውር እና መብራት ኖሮት ከG+1 ያልበለጠ ሲሆን በአክሱም ከተማ ይህንን ማሟላት የሚችሉ የቤት ባለቤቶች መሳተፍ ይችላሉ።
  1. ከያሬድ ዜማ ሆቴል እስከ ብራና ሆቴል ባለው መስመር ዋናው የአስፋልት መንገድ ግራና ቀኝ እስከ 200 ሜትር ገባ ብሎ
  2. ተወዳዳሪዎች የተጨማሪ እሴት ታክሰ /ቫት/ እና ቲኦቲ ተመዝጋቢዎች ከሆኑ የማስረጃውን ኮፒ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የሚሰጡትም ዋጋ ቫት እና ቲኦቲ ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን መግለፅ አለባቸው፤ ካልተገለፀ ከነቫት እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል።
  3. ተወዳዳሪዎች ቤቱ ህጋዊ ስለመሆኑና የዘመኑን ግብር የከፈለበት ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባችዋል እንዲሁም የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባችዋል።
  4. ተጫራቾች ለዚህ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2:00 እስከ 11:00 ድረስ ከሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀርበው በመግዛት የሚያከራዩበትን የአንድ ወር ዋጋ በመሙላትና በታሸገ ፖስታ ውስጥ በማድረግ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈተው ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣበ16ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 8:00 ተዘግቶ በዚያው ቀን 8:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል።
  • ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • አድራሻ፦ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሳያዊ ሪፐብሊክ በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
  • ስልክ ቁጥር፦ 034 775 3366