ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የተጋገረ የዳቦ አቅርቦት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት፡-
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ መሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ፣
- በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል፣
- ተጫራቹ ቲን ሰርተፊኬት ምዝገባ ማቅረብ የሚችል፣
- ተጫራቹ የማቅረቢያ መታወቂያ ምዝገባ ያለው መሆኑ ማቅረብ የሚችል፣ ሎት 1 የተጋገረ ዳቦ አቅርቦት፣ የጨረታ ማስከበሪያ 250,000.00 ብር በሲፒኦ ወይም በባንክ ጋራንቲ ማቅረብ የሚችል፣
- ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ 200.00 ብር /ሁለት መቶ ብር /በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላል፣
- ማንኛውም ተጫራች በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ማህተምና ፊርማ በማድረግ ማቅረብ አለበት፣
- ጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮበ16 ኛው ቀን በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን በ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፣
- ዩኒቨርሲቲው ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 09 14 70 31 20 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል።