Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Document No.: OF/EABC/MEK/

Issue No: 09-3/01-2/1198

Date 27/09/2017

ያገለገሉ ንብረቶች የወጣ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ፣

በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ የሚገኙ የተለያዩ ያገለገሉ ንብረቶች በጨረታ መሸጥ ይፈልጋል::

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2-10 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በቅ/ጽ/ቤቱ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የማይመለስ ብር 100.00(አንድ መቶ ብር)በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ

ጨረታው 04/10/2017 ዓ.ም ከሰዓት በፊት 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4፡15 ሰዓት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይከፈታል" ስለዚህ ሽያጭ አፈጻጸሙ በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን እየገለጽን፣ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ የጠቅላላ የጨረታ ዋጋውን 5% C P O ማስያዝ ይኖርባቸዋል"

ተጫራቾች ከላይ የተገለፀውን መጠን በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ። ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው" ለተጨማሪ ማብራሪያ በሚቀጥለው አድራሻ መጠቀም ይቻላል"

አድራሻ፣

❖ ሓሚዳይ ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ ፊት ለፊት