በኢትዩጵያ ቀይሕ መስቀል ማሕበር የትግራይ ቅርንጣ

ግልጽ የጨረታ ማስታወቅያ

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት በክልሉ ስር ላሉት ኣምስት መድሃኒት ቤቶች ኣገልግሎት የሚውሉ የካሽ ረጂስተር ማሽኖች ለመግዛት ከዚህ ማስታወቅያ ጋር ተያይዞ ባለው ስፔስፊኬሽን መሰረት በጨረታ ኣወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች 1

1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው

2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ/VAT/ የተመዘገባችሁ

4. በኣቅራቢነት የተመዘገባችሁ

5. የማይመለስ ብር 100.00(ኣንድ መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 10 በስራ ሰዓት ከ22/09/2017 ዓ/ም እስከ 06/10/2017 ዓ/ም መውሰድ ትችላላችሁ ።

6. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረብያ ሰነድ በትክክል ሞልታችሁ በማሸግ እስከ 06/10/2017 ዓ/ም 9:00 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ሰጥን ማስገባት ይቻላል ፤ በተጨማሪም ለውድድር ለጨረታ ያቀረባችሁት ዋጋ ለምን ያህል ግዜ እንደሚቆይ/Validity Period/ መጠቀስ ኣለበት ።

7. ተጫራቾች ኣስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች በታሸገ ቦታ ማቅረብ ኣለባቸው ።

8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ 10% ካቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ።በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ኣይፈቀድም ።

9. የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን 06/10/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ቢገኙ ይመረጣል ። ሆኖም ግን ባለመገኘታቸው ጨረታው ኣይስተጓጎልም ።

10. ኣሸናፊ ተጫራች ጨረታው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ 3 ቀናት ውስጥ ካሸነፉት ጠቅላላ ዋጋ 10% ሲፒኦ በማስያዝ ቀረቦ ውል ማሰር ግዴታ ኣለበት ።

11. ጽ/ቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ።

❖ ለተጨማሪ ማብራርያ በስልክ ቁጥር 0344408351 መደወል ይቻላል።