የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ሰነድ ቁጥር 006/2024/2025
ትራንስ ኢትዮዽያ ሃ/የ/የግ/ማሕበር መቐለ በሚገኘው ዋና ቢሮ ቤት በተለያዩ ቦታዎች የደህንነት ካሜራ (Security Camera) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ገዝቶ ለማስገጠም ስለ ፈለገ በዘርፉ የተሰማራቹ ኣቅራቢዎች ከዚህ በታች የተገለፁ ነጥቦች የምታማሉ ተጫራቾች በጨረታዉ እንድትሳተፉ እንጠይቃለን።
- ተጫራቾች በተጠቀሰው ዘርፍ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ ኣለባቸው፡፡ የ 2017 ዓ/ም ንግድ ፍቓድ ያላሳደሰ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል፡፡ የ2017 ዓ.ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ በዋናው (Original) ቴክኒካል ጨረታ ሰነድ ውስጥ ታሽጎ መቅረብ አለበት።
- ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን በግልፅ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡ይህ ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) እንዳካተተ ተደርጎ ይወሰዳል።
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ድርጅታች በሰጣቸው ፋይናንሻል ጨረታ ሰነድ ብቻ መሆን አለበት፣
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ሰነድ ስርዝ ድልዝ ያለበት መሆን የለበትም፡፡ ስርዝ ድልዝ ያለበት ሰነድ ያቀረበ ተጫራች ከውድድሩ ውጭ ይሆናል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ (Bid Bond) ባቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በትራንስ ኢ/ያ ኃ/የተ/የግ/ ማሕበር ስም የተዘጋጀ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው:: ጠቅላላ ዋጋ ማለት ያቀረቡት የሁሉም ዕቃዎች ድምር ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) ጨምሮ ማለት ነው፡፡የሚቀርብ ሲፒኦ ለብቻው ታሽጎ መቅረብ አለበት፡፡ ሲፒኦ ያላቀረበ ወይም በተጠቀሰው መጠን መሰረት ያላስያዘ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል።
- አሸናፊ የሆነ ተጫራች ላሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ (ተጫማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ) ውል ማስከበርያ (Performance Bond) 10% ማስያዝ አለበት።
- ተጫራቾች ፋይናንሻልና ቴክኒካል ጨረታ ሰነድ በመቐለ ዋና ቢሮ በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮ እንዲሁም በአዲስ አበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስየማይመለስ ብር 500በመክፈል መውሰድ አለባቸው፡፡
- ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ ጨረታው ከተከፈተ በኋላ እስከ ውል ሚታሰርበት ቀን ለ 90 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ መሆኑ ማወቅ ኣለባቸው።
- ተጫራቶች ኣሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀን ውስጥ ውል ማሰር ኣለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ ከሞምላታቸው በፊት እንዲሁም ጨረታው ከሚከፈትበት 5 ቀን በፊት ወደ መቐለ ቢሮ በኣካል በመምጣት እያንዳንዱ የደህንነት ካሜራ የሚገጠምበት ቦታ የማየት ግዴታ ኣለባቸው፡፡
- አሸናፊ የሆኑ ተጫራቶች መቐለ በሚገኘው ዋና ቢሮ ያሸነፉት ዕቃ በራሳቸው መጓጓዟ ማቅረብና መግጠም ኣለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ በታሸገ ፖስታ እስከ ግንቦት 12/2017 ዓ/ም ጠዋት ሰዓት 3:30 በመቐለ ዋና ቢሮ በዳይሬክተር ግዢና የአቅራቢዎች ትስስር ቢሮ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ፋይናንሻልና ቴክኒካል ፕሮፖዛል ኦርጅናልና ፎቶኮፒ ለየብቻ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ጨረታው ግንቦት 12/2017 ዓ.ም. ጠዋት 3:30 ሰአት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ጠዋት 4:00 ሰአት በመቐለ ዋና ቢሮ በዳይሬክተር ግዢና የአቅራቢዎች ትስስር ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታ ሰነድ በተቀመጠው የጨረታ ማስታወቅያ መሰረት የተሟላ ከሆነ ተጫራቾች ባይገኙም ይከፈታል።
- ድርጅታችን ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ ማብራርያ ወይም ግልፅ ያልሆነላቸው ሃሳብ ተጫራቾች በአካል በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 0914007732/0911867040 በሥራ ሰዓት ደውላቹ መጠየቅ ትችላላቹ።