የምሥራቃዊ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዓዲግራት ምድብ ችሎት

ማስታወቂያ

አፈ/ከሳሽ፡- ሕብረት ባንክ ኢማ

አፈ/ተከሳሾች፦

1, አቶ ቴድሮስ ተወልደ ኃይሉ

2. ወ/ሮ ብርትኳን ዘመነ አዳነ መካከል ባለው የአፈፃፀም ክርክር በ1ኛ አፈ/ተከሳሽ ስም የሚታወቅ በ ጋንታ አፈሹም ወረዳ ቡከት ቀበሌ መንደር አጎሮ የሚገኝ፤ አዋሳኙ በምስራቅ መቐለ- ዓዲግራት አስፋልት መንገድ፣ በምዕራብ ዲንጋያማ ቦታ፣ በሰሜን የአረጋውያን መጦርያ ቦታ በደቡብ የቀበሌ ድብላ ስዔት ቦታ የሆነ በ0.32 ሄክታር የተሠራ ብሌን ፔትሮሌም በመባል የሚጠራ የአፈ ተከሳሾች የነዳጅ ማደያና ዲፖ ድርጅት፤ የሊዝ ዘመኑ ከ26/3/2009 ዓ.ም ጀምሮ ለ50 ዓመት የተወሰደ፤ በመነሻ ዋጋ ብር 48,669,896.28 (አርባ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ከ28/100) በጨረታ ተሸጦ ለዕዳ መከፈያ እንዲውል ስለተፈለገ ለጨረታ እንዲወጣ ታዟል።

በዚህ መሰረት፡-

  1. ጨረታ የሚካሄድበት ቦታ በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የአዲግራት ምድብ ችሎት ሆኖ የጨረታ ሰነዱ ታሽጎ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ሳጥን የሚገባ ይሆናል።
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ወደ ሳጥን ከማስገባታቸው በፊት ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን ጨረታው ካላሸነፉ የሚመለስ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺ)በቼክ ወይም በጥሬ-ገንዘብ ያስይዛሉ።
  3. የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈበት የንብረቱን ዋጋ 25% ወድያውን በቼክ ለጨረታ ኮሚቴው የሚያስይዝ፣ የቀረው 75% ደግሞ ጨረታው ካሸነፈ በ15 ቀን ውስጥ ገቢ ያደርጋል። በተባለው 15 ቀን ክፍያ ካልፈፀመ ያስያዘው ጨረታ ማስከበርያ ገንዘብ ለመንግሥት ገቢ ሆኖ ጨረታው የሚሰረዝ ይሆናል።
  4. ጨረታ የሚካሄድበት ቀን 16/9/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00-5፡00 ሆኖ ልክ ከቀኑ 5፡10 የጨረታ ሳጥኑ ተከፍቶ የጨረታው ውጤት ማሳወቅ የሚጀምር ይሆናል።

የምሥራቃዊ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዓዲግራት ምድብ ችሎት