ግልጽ የጨረታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር : የትግራይ ክልል _ ቅ/ጽ/ቤት አዲስ ጎማ በቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት ለፍሳሽ ማሰወገጃ ተሽከርካሪ አገልግሎት የሚውሉ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቶች፡-

1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ

2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገባችሁ

4. በአቅራቢነት የተመዘገባችሁ

5. የማይመለስ ብር 5000 በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 10 በስራ ሰዓት ከ5/07/2017ዓ/ም እስከ 19/07/2017ዓ/ም መውሰድ ትችላላችሁ

6. ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በትክክል ሞልታችሁ በማሸግ እስከ 19/07/2017 ዓ/ም ሰዓት 9፡00 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ለውድድር ለጨረታ ያቀረባቹሁት ዋጋ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ /validity period/ መጠቀስ አለበት፡፡

7. ተጫራቶች አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡

8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ 2% ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ኣይፈቀድም፡፡

9. የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን 19/07/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ቢገኙ ይመረጣል፡፡ ሆኖም ግን ባለመገንኘታቸው ጨረታው አይስተጓገልም፡፡

10. አሸናፊ ተጫራች ጨረታው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውስጥ ካሸነፉት ጠቅላላ ዋጋ 10% ሲፒኦ በማስያዝ ቀርቦ ውል የማሰር ግዴታ አለበት

11. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥር -- 0344-408351 መደወል ይችላል፡