የጨረታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት 1ኛ ለአቶ አታኸልቲ ሐጎስ ገ/ዝጊ እንዲሁም 2ኛ. ለገነት ጠብታ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለሰጠው ብድር አመላለስ በዋስትና የያዘውን ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/11 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል::

የተበዳሪው/ መያዣ ሰጪው ሰምየመያዣ ንብረቱ አድራሻለጨረታ የቀረበ ንብረት ዓይነትና ዝርዝርየቦታው ስፋት በካ/ሜየጨረታው መነሻ ዋጋ /በብርየጨረታው ደረጃጨረታየሚከናወንበት ቀን እና ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌ ‌‍‍‍‌‍
አቶ አታኽልቲ ሓጎስ ገ/ዝጊበትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን አከሱም ከተማ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር 7299/ድ/2016 የሆነየሆቴል ድርጅት ህንፃዎች እና የሆቴል መገልገያ ቁሳቁሶች4552.74ብር 27,806,388.86 /ሀያ ሰባት ሚሊዮን ስምንት መቶ ስድስት ሺህ ሦስት መቶ ሰማንያ ስምንት ብር ከ86 ሣንቲም/የመጀመርያ ጨረታጥር 27 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00-6:00
የገነት ጠብታ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የቲማቲም ማቀናበርያ ፋብሪካ ህንፃ እና ማሸነሪዎችበትግራይ ክልል አድዋ ከተማ ደበርቺ ቀበሌ ህንፃ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር 2969/2005 የሆነ ማሽነሪዎች እና አይሱዙ ተሽከርካሪ ሞዴል NPR71H26የቲማቲም ማቀነባበርያ ፋብሪካ3500ካ/ሜብር 10,558,627.77/አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ ስምንት ሺህ ስድስት መቶ ሃያ ሰባት ብር ከ77 ሣንቲምየመጀመርያ ጨረታጥር 28 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00–6:00

ማሳሰቢያ፡-

  1. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የመያዣ ንብረት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ንብረቱን የሚገዙበትን ዋጋ፣ ስምና አድራሻቸውን በመጥቀስ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት የአታኽልቲ ሓጎስ ገ/ዝጊ ሆቴል ድርጅት እስከ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት ድረስ እንዲሁም የገነት ጠብታ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የቲማቲም ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እስከ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ 1/4 በባንክ ክፍያ ማዘዣ /ሲ.ፒ.ኦ/ ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡
  3. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ15 /በአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡
  4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ በተመለከተው ቀንና ሰዓት በኢትዮጵያ ልማት ባንከ መቐለ ዲስትሪክት ፅሕፈት ቤት ይካሄዳል፡፡
  5. በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልፅ ደብዳቤ ከባንኩ ሲደርሰው አሸናፊ ይሆናል።
  6. የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸው ተሽከርካሪ እና ማሽነሪዎችን በተመለከተ ገዢው የቀረጥ ነፃ መብት ሊኖረው ይገባል ወይም በንብረቶቹ ላይ በመንግስት የሚፈለገውን ቀረጥና ታክስ ለመክፈል ይገደዳል፡፡
  7. ባንኩ ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች የሚሸጠው ከተቻለ ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን አሸናፊው በባንኩ ብድር ፖሊሲና የአሰራር ስርዓት መሠረት አስፈላጊውን መስፈርቶች ካሟላና ፕሮጀክቱን የሚያስቀጥል ከሆነ ንብረቱን በከፊል ብድር ለመግዛት መጠየቅ ይችላል፡፡
  8. በጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው፡፡
  9. የንብረቱ ስመ ንብረት ለገዢው እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል። ገዢው ጉዳዩን ተከታትሎ ያስፈፅማል።
  10. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች የሽያጩን 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ከፍያዎች፣ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ይከፍላል።
  11. በጨረታው ዝርዝር እና ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪከት በሚገኘው ሎን ሪቨው ዲቨዥን በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 09-14-70-33-62/09-42-70–79–20 (034 440 7439 ፣ 034 441 9016) ደውሎ ማግኘት ይቻላል፡፡ ንብረቱን መጐብኘት የሚፈልግ ከዲቪዥኖቹ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጐብኘት ይቻላል፡፡
  12. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት