የሰሜን ሪጅን የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ

ግልጽ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏

በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ሰሜን ሪጅን የዓዲግራት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ህንፃ በግልጽ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ።

ከ16 እስከ 20 ክፍል ወይም ከ200 እስከ 250 ካሬ ሜትር ሆኖ ለቢሮ አቀማመጥ እና አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ የሆነ

  • የእያንዳንዱ ክፍል ስፋት ቢያንስ 3x4m2 እና ከዚያ በላይ የሆነ
  • እንዲሁም ቤቱ ውሃ መብራት እና ሽንት ቤት ኖሮት ከ G+1 በላይ መሆን የሌለበት ሲሆን በዓዲግራት ከተማ ይሄንን ማሟላት የሚችሉ ቤቶች መሳተፍ ይችላሉ።

1.1. ከፒያሳ እስከ ዋናው ቴሌ ግራና ቀኝ እስከ 200ሜ ገባ ብሎ

1.2. ከፒያሳ እስከ ሞቢል ማደያ ግራና ቀኝ እስከ 200ሜ ገባ ብሎ

  • ተወዳዳሪዎች የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ እና ቲኦቲ ተመዝጋቢዎች ከሆኑ የማስረጃውን ኮፒ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የሚሰጡትም ዋጋ ቫት እና ቲኦቲን ያካተተ ወይንም ያላካተተ መሆኑን መግለጽ ያለባቸው ሲሆን ይህ ካልተገለጸ ግን የሰጡት ዋጋ ቫት እና ቲኦቲ ያካተተ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል።
  • ተወዳዳሪዎች ቤቱ ህጋዊ ስለመሆኑና የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል እንዲሁም የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች ለዚህ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ የተዘጋጀውን የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ የማይመለስ 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 11፡00 ድረስ ከሰሜን ሪጅን የዓዲግራት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀርበው በመግዛት የሚያከራዩበትን የአንድ ወር ዋጋ በመሙላትና በታሸገ ፖስታ ውስጥ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  • ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው የሚከፈተው ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ በ16ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 8፡00 ተዘግቶ በዚያው ቀን 8፡30 ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል።
  • ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • አድራሻ:- በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሳያዊ ሪፐብሊክ በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሰሜን ሪጅን ዓዲግራት ቅ/ጽ/ቤት

ስልክ ቁጥር፡- 034 245 8636

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሰሜን ሪጅን ዓዲግራት ቅ/ጽ/ቤት