የሃራጅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 16/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መጋዝን ውስጥ የሚገኙትን የተለያዩ ለአራተኛ ግዜ የወጡ የተሽከሪካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ብትን ጨርቅ በሃራጅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መሳተፍ ይችላል፡፡
1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይነሩባቸዋል፡፡
2. ከላይ በተ.ቁ 1 በተገለፀው ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ቢኖርም የመነሻ ዋጋቸው ከብር 500,000 በታች የሆነ ማንኛውም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት እንዲያቀርብ አይገደድም፡፡
3. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000012078537 ገቢ በማድረግ የባንክ አድቫይሱን በመያዝ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመሄድ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመሄድ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ሃምለ 13/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሃምለ 18/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ድረስ የተጠቀሱት ማስረጃዎች ኮፒ በማቅረብ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል፡፡
4. በሃራጅ ጨረታው ለመሳተፍ ተጫራቾች ለተሸከሪካሪ መላዋወጫ እቃዎች ብር 100,000 ለብትን ጨርቅ ብር 522,706 ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ (C.P.O) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ፡፡
5. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
| የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንብረቱ ዓይነት | ጨረታው ዓይነት | የንብረት መመልከቻ ቀን የጨረታ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮ | የጨረታው የመዝጊያ እና የመክፈቻ ቀንና ሰዓት | |
|---|---|---|---|---|---|
| ከ | እስከ | ||||
| መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት | የተለያዩ እቃዎች | ግልጽ ጨረታ | 13/11/2018 | 18/11/18 | 18/11/2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡15 ጀምሮ ጨረታው ይካሄዳል፡፡ |
6. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።
7. ለጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
8. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ስለ ማሸነፋቸው ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉት የዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
9. ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡
10.በጨረታ የሚሸጠው ዕቃ በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፣ ወኪል ፤ ባለቤት ወይም ቤተሰብ የነበረ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም፡፡
11.ተጫራቾች የሚሰጡት ዋጋ ከቫት በፊት መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡
12. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል።
13 ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን፡፡