የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምርያ ማህበር

የተለያዩ ያገለገሉ ቋሚ ንብረቶችን በግልጽ ጨረታ ለመሸጥ የወጣ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማህበር በኢፈድሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ማቋቋሚያ አዋጅ 1113/2011 በመዝገብ ቁጥር 0475 ተመዝግቦ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሀገር በቀል ድርጅት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ ከተለያዩ ረጂ ድርጅቶች በሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ለዓላማው ማስፈጸሚያ ይረዳው ዘንድ የተለያዩ ቋሚ ንብረቶችን የሚገዛ ሲሆን የአገልገሎት ዘመናቸው ሲጠናቀቅ ማቋቋሚያ አዋጁ ባስቀመጠው የንብረት አወጋገድ ሥረዓት መሠረት እንዲወገዱ ያደርጋል በዚሁም መሠረት ማህበሩ ባለቤትነት የያዛቸውና የአገልገሎት ዘመናቸው ያበቁ የተለያዩ ቋሚ ንብረቶችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

በመሆኑም በሚከተሉት ሁኔታዎች መሠረት ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች፣ ድርጅቶች እና ተቋማት የዋጋ ማቅረቢያ እንዲያቀርቡ ይጋብዛል።

1. የሚሸጡንብረቶች

+ የተለያዩ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች፣

+ የኮምፒዩተርና የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣

+ የህክምና አገልግሎት መስጫ መሳሪያዎች

+ የመኪና ጎማ እና

+ ሌሎችያገለገሉ ቋሚ ንብረቶች

2. ተጫራቶች ሊያሟሉዋቸው የሚገቡ ነገሮች

+ በአሮጌ እቃ ግዥና ሻጭ ዘርፍ ህጋዊ የ ዘመኑ ታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቹሁ፣

+ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቹሁ፣

+ አሸናፊ ከታወቀ በሃላ ንብረቱ በ3 ቀን ጊዜ ውስጥ ማንሳት የሚችል፣

+ የጨረታ ውል ማስከበርያ ብር 5,000.00 ከአዋሽ ባንክ ሲፒኦ አሰርቶ ማቅረብ የሚችል ፣

3. የንብረትመመልከቻጊዜ

በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ከ14/11/2018 ዓ/ም እስከ 25/11/2018 ዓ/ም ድረስ በሚከተለው አድራሻን ብረቶቹን መመልከት ይችላሉ።

አድራሻ፡

በኢትዮጵያቤተሰብመምሪያማህበር

ሰሜን አካባቢ ጽ/ቤት ሓወልቲ ክከተማ/ቀበሌ | መቀለ ከተማ ደጀን ቢሮ አጠገብ ወደ ዓዲ ሹም ድሑን በሚወሰደው ኮብል ስቶን ገባ ብሎ ይገኛል

ተጫራቾች በተጠቀሱት የመመልከቻ ቀናት ከላይ በተገለጹት አድራሻዎች ዘወትር ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 10:00 ንብረቶቹን በአካል መመልከት ይችላሉ፡፡

4. የጨረታ ማቅረቢያ ሁኔታ

ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በጽሁፍ መቅረብ ያለበት ሲሆን ድርጅቱ ለዚሁ ተግባር ይረዳቸው ዘንድ ያዘጋጀውን የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የማይመለስ ብር 100:00 (አንድ መቶ ብር ብቻ) በመክፈል በመግዛት፤ለሚጫረቱበት ማናኛውም ቋሚ ንብረት የነጠላ ዋጋ እና የንብረቱን መለያ ቁጥር በትይዩ በዚሁ ቅጽ ላይ በመሙላትና በፖስታ በማሸግ የተጫራቹን ግለሰብ/ድርጅት ሙሉ ስም፣ አድራሻ እና የስልክ ቁጥር በፖስታው ላይ በመመዝገብ መሆን አለበት።

4. የጨረታ ማስገቢያ ቀንና ሰዓት

ማንኛውም ተጫራች ግለሰብ/ድርጅት ያዘጋጀውን የጨረታ 25/11/2018ዓ/ም ከ ጥዋቱ 4:00 ሰዓት በፊት በሚከተለው አድራሻ ድርጅቱ ለዚሁ አገልግሎት ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ መክተት አለበት፡፡

በኢትዮጵያቤተሰብመምሪያማህበር

ሰሜን አካባቢ ጽ/ቤት ሓወልቲ ክፍለ ከተማ/ቀበሌ

መቀለ ከተማ ደጀን ቢሮ አጠገብ ወደ ዓዲ ሹም ድሑን በሚወስደው ኮብል

5. የጨረታመክፈቻ

ጨረታው በ 25/11 /2018 /ም ከጥዋቱ ልክ በ 4:30 ሰዓት በድርጅቱ ጽ/ቤትይከፈታል።

6. ልዩ ማስታወሻ

- ድርጅቱ የተሻለ የዋጋ አቅርቦት ያቀረበውን ተጫራች ለመምረጥ መብት አለው።

- ድርጅቱ ማንኛውንም ወይም ሁሉንም የዋጋ አቅርቦቶች የመቀበል ወይም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪመረጃ፦

ስልክ፡ 0344418342 ይደውሉ