የዕቃዎች ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
ቁጥር 13/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜያት ተይዘው ውርስ የተደረጉ ብትን ጨርቅ እና የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ እንዲሁም የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ለ3ተኛ ጊዜ ፣ የቤትና የቢሮ እና የንጽሕና ዕቃዎች ደግሞ ለ2ተኛ ጊዜ የወጡ ዕቃዎች በሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ መሽጥ ይፈልጋል።
1) በመሆኑ ቅ/ጽ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ሀ) በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ የምስከር ወረቀት /ክሊራንስ/ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በፖስታ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖሩበታል፡፡ ለሐራጅ ደግሞ የጨረታ ሰነዱ በጨረታ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአካል ይዞ መቅርብ አለበት።
ለ) የዚህ አንቀጽ ፊደል ተራ(ሀ) ድንጋጌ ቢኖሩም ግምታዊ ዋጋ ከብር 500ሺህ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም።
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡ዐዐ ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ በሒሳብ ቁጥር 1000012078537 በመክፈል ደረሰኝ ከጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 እንዲሁም የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 411 በመምጣት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት በአካል በመሄድ ሰነዱ መግዛት ይቻላል።
3. ተጫራቾች ማስታወቂያ በጋዜጣው ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር እስከ 7ተኛ ቀን ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ናሙና በጽ/ቤቱ ውርስ መጋዘን በአካል እየሄዱ መመልከት ይችላሉ።
4. ጨረታው የሚካሄደው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ8ተኛው ቀን ሲሆን ጨረታው ከጠዋቱ 3፡00 (ሶስት ሰዓት) ተዘግቶ 3፡15 ( ሶሰት ሰዓት ከአስራ አምስት ደቂቃ ) ይከፈታል፡፡ እንዲሁም ሐራጅ ጨረታው ደግሞ በተመሳሳይ ቀን ከ4፡00 ( አራት ሰዓት) ጀምሮ ይካሄዳል።
5. ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተገለፀው ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 8ተኛው ቀን የሥራ ቀን ሳይሆን ሲቀር ጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።
6. ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደርባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ(5%) እንዲሁም በሐራጅ ለሚሸጡ ዕቃዎች በየኮዱ የሚለያይ ስለሆነ ከጨረታ ሰነድ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የጨረታ ማስከበሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ ስም ETHIOPIA customs commission mekelle branch office በሚል በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይጠበቅባችል።
7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ጽ/ቤቱ የመሰብሳብያ አዳራሽ 4ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 ይካሄዳል።
8. ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና የጨረታ ውጤት በተገለጸው በ3 (ሰሶት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት።
10. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ከፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የዕቃው ዋጋ ገቢ አድርጎ ዕቃው በሁለት ወር ውስጥ ካልወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል።
11. በጨረታ የሚሸጠው በተቆሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፤ ወኪል፤ ባለቤት ወይም ቤተሰብ በማንኛውም መልኩ በጨረታ መሳተፍ አይችልም።
12. ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ
መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን።
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት