ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት

ግልጽ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 12/2018

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜያት ተይዘው ውርስ የተደረጉ

  • አልባሳት፣
  • ጫማዎች እና
  • የተሸከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

በመሆኑ ቅ/ጽ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

ሀ) በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ የምስክር ወረቀት /ክሊራንስ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በፖስታ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖሩበታል፡

ለ) የዚህ አንቀጽ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖሩም ግምታዊ ዋጋ ከብር 500ሺህ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም።

2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ2፡ዐዐ ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000012078537 በመክፈል ደረሰኝ ከጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 እንዲሁም የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 411 በመምጣት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመሄድ ሰነዱ መግዛት ይቻላል።

3. ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር አስከ 7ተኛ ቀን ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ናሙና በጽ/ቤቱ ውርስ መጋዘን በአካል እየሄዱ መመልከት ይችላሉ።

4. ጨረታው የሚካሄደው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ8ተኛ ቀን ሲሆን ጨረታው ከጥዋቱ 4:00 (አራት ሰዓት ተዘግቶ 4፡15 (አራት ሰዓት ከአስራ አምስት ደቂቃ) ይከፈታል።

5. ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተገለፀው ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 8ተኛው ቀን የሥራ ቀን ሳይሆን ሲቀር ጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።

6. ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደርባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ (5%) የጨረታ ማስከበሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ ስም ETHIOPIA customs commission mekelle branch office በሚል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰርተው ማስያዝ ይጠበቅባችል።

7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ፅ/ቤቱ የመሰብሳብያ አዳራሽ 4ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 ይካሄዳል።

8. ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና የጨረታ ውጤት በተገለጸው በ3 (ሰሶት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል።

9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት።

10. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረከበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የዕቃው ዋጋ ገቢ አድርጎ ዕቃው በሁለትወር ውስጥ ካልወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል፡

11. በጨረታ የሚሸጠው በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ፣ ወኪል፤ ባለቤት ወይም ቤተሰብ በማንኛውም መልኩ በጨረታ መሳተፍ አይችልም።

12. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251 34 240 7107 ወይም +251 34 240 8513 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን።

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት