የግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ ቁጥር 11/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መጋዝን ውስጥ የሚገኙትን የተለያዩ እቃዎች የምግብ ነክ እቃዎች ፤ በርበሬናቅመማቅመም፤ጨርቃጨርቅና ጫማዎች የስፔርፓርት እቃዎች የህንፃ መሳርያዎች፣የብረታ ብረት እቃዎች የንፅህና መጠበቅያ አቃዎች፤የኤሌክትርክ ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መሳተፍ ይችላል፡፡
1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ሰረቲፊኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ የሚችል፡፡
2. ተጫራቾች በጨረታው ለመመዝገብ ሲመጡ ከላይ በተ.ቁ 1 የተገለፁት ሰነዶች ኦርጅናል እና ኮፒ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3. ከላይ በተ.ቁ 1 የተገለፀው ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ቢኖርም ግምታዊ ዋጋቸው ከብር 500,000 በታች የሆነ ማንኛውም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት እንዲያቀርብ አይገደድም፡፡
4. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/በመክፈል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉምሩክ ኮሚሽን መቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000012078537 ገቢ በማድረግ የባንክ አድቫይሱን በመያዝ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመሄድ የመ/ቤቱ ደረሰኝ ከተቆረጠላቸው በኃላ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመሄድ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከመጋቢት 04/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ከመጋቢት 14/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ድረስ የተጠቀሱት ማስረጃዎች ኮፒ በማቅረብ የጨረታ ሰነድ መግዛት
5. በግልፅ ጨረታው ለመሳተፍ ተጫራቾች ዕቃው ለመግዛት የሚያቀርቡትን የመጫረቻ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ (C.P.O) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ ለዘመናዊ ፍትሓዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት ግንባታ ተግተን እንሰራለን!!
6. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
| የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንገረሉ ዓይነት | ጨረታው ዓይነት | የንብረት መስክ ቀን የጨረታ ሰነድ ከዱ ቀን ጀምሮ | የጨረታ ሰሚያ እና ፈቻ ቀንና ሰዓት | |
|---|---|---|---|---|---|
| ከ | እስከ | ||||
| መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት | የተለያዩ እቃዎች | ሃራጅ ጨረታ | 04/07/2018 | 14/07/2018 | ጨረታው 14/07/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን 6:30 ይከፈታል፡፡ |
6. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት ሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
7. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት ሂካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
8. በጨረታ ተወዳድረው ለተሸነፉ ተጫራቾ ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉት የዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
10.ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው
11. በጨረታ የሚሸጠው ዕቃ በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃው አስመጪ ፣ ወኪል ፣ ባለቤት ወይም ቤተሰብ የነበረ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም፡፡
12. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ 13.ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆነ እንገልፃለን፡፡